በዲጂታል ብር ዙሪያ ጥናት መጀመሩ ተነገረ

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በገንዘብ ዘርፍ እየታየ ያለውን ዓለም አቀፍ ለውጥ ተከትሎ “የማዕከላዊ ባንክ ዲጂታል ገንዘቦችን” በተመለከተ ጥናት በማድረግ ላይ መሆኑን አስታወቀ።

የብሔራዊ ባንክ ገዥ እዮብ ተካልኝ (ዶ/ር) ዲጂታል ግብይቶች በእጅጉ እያደጉ ቢሄዱም፣ ጥሬ ገንዘብ አጠቃቀም ሙሉ በሙሉ አይጠፋም የሚል እምነት እንዳላቸው ገልጸዋል።

“ምናልባትም ዲጂታል ግብይቶች በጥልቀት የሚሰፉበት እና በከፍተኛ ደረጃ የሚያድጉበት፣ ነገር ግን ለጥሬ ገንዘብ ግብይቶችም ምቹ ሁኔታ የሚኖርበት ባለ ሁለት ገፅታ መዋቅር ሊኖር ይችላል ብለን እንጠብቃለን” ያሉት ገዢዉ፣ “በእኛ ሀገር ከፍተኛ መጠን ያለው መደበኛ ያልሆነ ኢኮኖሚ፣ የገጠሩ ዘርፍ እና ሌሎችም አሉን። ስለዚህ የገንዘብ ግብይቶች ይቀጥላሉ ብዬ እጠብቃለሁ” ብለዋል።

እዮብ ተካልኝ ፤ በተለይም ወደ አዲሱ የፋይናንስ ዓለም በሚደረገው ሽግግር፣ ማዕከላዊ ባንኮች በዲጂታል ዘመን ለገጠማቸው ከባድ ፈተናዎች እውቅና ሰጥተዋል።

“ማዕከላዊ ባንኮች አሁን የማዕከላዊ ባንክ ዲጂታል ገንዘቦች ምን እንደሆኑ መረዳት አለባቸው.. ያ ገንዘብ የተለየ መልክ ሊይዝ ይችላል፣ ግን አሁንም ያ ገንዘብ ይኖራል” ብለዋል። በጉዳዩ ላይ ብሔራዊ ባንክ ጥናት እያካሄደ መሆኑን አረጋግጠው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...