በ31ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ የማንቹርያን ደርቢ ይጠበቃል

Date:

በ31ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ መርሀ ግብር በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ሲደረጉ ማንችስተር ዩናይትድ ከማንችስተር ሲቲ የሚያደርጉት የማንቹርያን ደርቢ ተጠባቂ ሆኗል፡፡

31ኛ ሳምንት የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጨዋታዎች ከነገ ጀምረው ሲካሄዱ ነገ 8፡30 ላይ በጉዲሰን ፓርክ ኤቨርተን ከአርሰናል በሚያደርጉት ግጥሚያ ጅማሮውን ያደረጋል፡፡

ብራዚላዊውን ተከላካይ ጋብርኤል ማጋሀሌስን እስከ ውድድር አመቱ መጨረሻ በጉዳት ያጡት መድፈኞቹ በቶፊሶቹ ሊፈተኑ እንደሚችሉ ሲጠበቅ በሳምንቱ አጋማሽ በፉልሀም ላይ ያስመዘገቡትን ድል ለመድገም ይፋለማሉ፡፡

እሁድ የሊጉ መሪ ሊቨርፑል ፉልሀምን ከሜዳው ውጭ ወደ ክራቨን ኮቴጅ አቅንቶ 10፡00 ላይ ሲገጥም ብራዚላዊው ወሳኙ ግብ ጠባቂ አሊሰን ቤከር ወደ ቋሚ 11 እንደሚመለስ ይጠበቃል፡፡

ቀያዮቹ ከፊታቸው የሚጠብቋቸውን 4 ጨዋታዎች ማሸነፍ ከቻሉ ሻምፒዮን መሆናቸውን ያረጋግጣሉ፡፡

በተመሳሳይ ሰአት በሳምንቱ አጋማሽ ቶተንሃምን በመርታት 4ኛ ደረጃ ላይ የሚገኘው ቼልሲ ወደ ጂቴክ ኮምዩኒቲ ስታድየም አቅንቶ ለታላላቅ ክለቦች ፈታኝ የሆነው ብሬንትፎርድን ይገጥማል፡፡

ምሽት 12፡30 ላይ የሳምንቱ ታላቅ ጨዋታ ኦልድትራፎርድ ላይ ሲደረግ በማንቹርያን ደርቢ ማንችስተር ዩናይትድ የከተማ ተቀናቃኙ ማንችስተር ሲቲን ያስተናግዳል፡፡

በቁርጭምጭሚት ጉዳት ለ7 ሳምንታት ያህል ከሜዳ የራቀው ኖርዌያዊው የማንችስተር ሲቲ አጥቂ አርሊንግ ሀላንድ ከጨዋታው ውጭ መሆኑን አስቀድሞ መዘገቡ ይታወሳል፡፡

ማንችስተር ዩናይትድ ለጨወታው የትኬት ዋጋ ቅናሽ ማድረጋቸውን ተዘግቧል፡፡

ሀገሬ ቲቪ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ኔታንያሁ እና ትራምፕ የፊታችን ማክሰኞ በዋይት ሀውስ እንደሚወያዩ ተገለጸ

የእስራኤል ጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት፤ ቤንያሚን ኔታንያሁ ከፕሬዝዳንት ዶናልድ...

አሜሪካ በኢትዮጵያ ያላትን የንግድና ኢንቨስትመንት ትብብር ለማጠናከር ከኢትዮጵያ መንግሥትና ከግሉ ዘርፍ ጋር ውይይት አካሄደች

በኢትዮጵያ የአሜሪካ አምባሳደር ኤርቪን ጄ. ማሲንጋ፣ ከኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ኮሚሽን...

የካፍ ፕሬዝዳንት የ2027 አፍሪካ ዋንጫ በ24 ተሳታፊ ሀገራት እንደሚካሄድ አስታወቁ

የአፍሪካ እግር ኳስ ፌዴሬሽን (ካፍ) ፕሬዝዳንት ፓትሪስ ሙትሰፔ የ2027...

የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ነፃ የጤና ምርመራና ሕክምና መስጠት ጀመረ

ሆስፒታሉ በቀን ከ300 በላይ ታካሚዎችን ያስተናግዳል የቅዱስ ጴጥሮስ ሆስፒታል ከሐምሌ...