ባለፉት 5 ዓመታት የኢትዮጵያ መንግሥት ወጪው ከገቢው በከፍተኛ ደረጃ በልጧል

Date:

የኢትዮጵያ መንግሥት ባለፉት 5 ዓመታት ያወጣው ወጪ ከሚያገኘው ገቢ በከፍተኛ ደረጃ መብለጡን የኢትዮጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር አስታውቋል።

የኢትየጵያ ኢኮኖሚክስ ባለሙያዎች ማህበር በዛሬው ዕለት 22ኛውን ዓለም አቀፍ ጉባዔ ያካሄደ ሲሆን፤ በመድረኩም ከወቅታዊ የሀገሪቱ ኢኮኖሚ ጉዳይ ጋር በተያያዘ ጥናታዊ ፅሁፎች ቀርበዋል።

በቀረበው ጥናትም የኢትዮጵያ መንግሥት ወጪው ከሚያገነው ከገቢ በከፍተኛ ደረጃ የበለጠ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በተቃራኒው መንግሥት ገቢው ከወጪው አንፃር አነስተኛ መሆኑን የገለጹት የማህበሩ ከፍተኛ ተመራማሪ ዶክተር አረጋ ሹመቴ፤ በጥናቱ ‘የመንግሥት ወጪ አቅጣጫ ወዴት የሚያመዝን ነው?’ የሚለውም መጠናቱን ገልጸዋል፡፡

“በከፍተኛ ሁኔታ የመንግሥት ካፓታል ወጪ መቀነሱም በጥናቱ ተረጋግጧል” ብለዋል፡፡

“ከ2016 ዓ.ም በፊት የመንግሥት ወጪ ትልቁን መደበኛ በጀት እየያዘ ኢንቨስትመንት እየቀነሰ መሄዱ ማሳያ ነው” ያሉት ዶክተር አረጋ “መንግሥት ትልቁ ኢንቨስተር ቢሆንም የሚጠበቀውን ያህል ግን ኢንቨሰት እያደረገ ለካፒታል በጀትም እየተያዘ አይደለም” ሲሉ ጠቁመዋል።

ሌላው ትኩረት የተደረገበት ጥናት የመንግሥት ዕዳ ላይ የሀገር ውስጥም ሆነ የውጭ ዕዳ ከፍተኛ መሆኑ ተገልጿል፡፡

በመድረኩም “ማንኛውም ሀገር ዕዳ አለበት” የተባለ ሲሆን፤ ዕዳው ከሀገር ውስጥም ሆነ ከውጪ ሊሆን እንደሚችል ተናግረዋል።

ይሁን እንጂ ኢትዮጵያ ከፍተኛ ዕዳ ያለበት የውጭ ዕዳ በመሆኑና ዕዳውም የመጣው በመንግሥት በራሱ እና የመንግሥት ተቋማት እንደ ኤልፓ፣ ቴሌኮም እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ የመሳሰሰሉ ተቋማት ናቸው ብለዋል፡፡

በተመሳሳይ መልኩ ጥናቱ የኢትዮጵያ ዕዳ የመክፈል አቅሟም ለመመለከት የተሞከረ ሲሆን፤ ዕዳ የመክፈል አቅም የሚለካው ወደ ወጪ በሚላክ ምርት ጋር የተያያዘ መሆኑ ተገልጿል፡፡

የኢትዮጰያ ዕዳ ከፍተኛው የውጭ ዕዳ በመሆኑ መለኪው ወደ ወጪ የሚላከው ምርቷ መሆኑ የተገለጸም ሲሆን፤ በዚህ አንፃር ሀገሪቱ ብዙ የውጭ ዕዳ አለባት ተብሏል፡፡ የሚካሄደዉ ጉባኤ እስከ ነገ የሚቀጥል መሆኑም ተገልጿል፡፡

(አሐዱ ሬዲዮ)

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...