ብዕርና ባሩድ በአሜሪካ በካናዳና በአውሮፓ ገበያ ላይ ዋለ

Date:

በጀርመን ፍራንክፈርት ከተማ አያሌ ኢትዮጵያውያን በተገኙበት በደማቅ ሥነ ሥርዓት የተመረቀው የአንዱዓለም አራጌ አዲስ መጽሐፍ ብዕርና ባሩድ በአሜሪካ ታትሞ በተለያዩ ከተሞች ለገበያ ቀርቧል።

ብዕርና ባሩድ በአሁኑ ወቅት በዋሽንግተን ዲሲ፣ በሲልቨር ስፕሪንግ፣ በቨርጂኒያ፣ በሂውስተን፣ በዴንቨር፣ በዳላስ፣ በኦክላንድና ሳንሆዜ በሽያጭ ላይ ይገኛል።

በተጨማሪም በካናዳ ቶሮንቶ ለአንባቢዎች ደርሷል።

በአውሮፓ ደግሞ በጀርመን ፍራንክፈርትና በርሊን፣ በስዊዘርላንድ፣ በሆላንድ አምስተርዳም እንዲሁም በስዊድን ስቶክሆልም ለአንባቢዎች መቅረቡ ታውቋል።

ይህ አዲስ መጽሐፍ የኢትዮጵያን የፖለቲካ ሰንሰለት በጥልቀት የሚፈትሽና ብዙ የሚያወያዩ ቁምነገሮችን የያዘ ሲሆን፣ ለሀገራዊ ችግሮች ዘላቂ መፍትሄዎችን የሚያመለክት ድንቅ ሥራ መሆኑ ተገልጿል።

መጽሐፉን በኢትዮጵያ ገበያ ለማቅረብ ዝግጅት እየተደረገ ሲሆን፣ በዓለም አቀፍ ደረጃ ለሚገኙ የአንላይን ተጠቃሚዎችም በቅርቡ በአማዞን ላይ እንደሚጫን ተጠቁሟል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...