የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አሜሪካ ከትናንት ጀምሮ ተግባራዊ ማድረግ ጀመረችውን ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረግ የጉዞ እገዳ “አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው” በማለት አወገዘ።
ውጤት ያልተገኘበት የአሜሪካ እና ኢራን ንግግር ፓኪስታን ውስጥ ከተካሄደ ከአንድ ቀን በኋላ የፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ አስተዳደር ወደ ኢራን ወደቦች ጉዞ እንዳይደረግ ዘግቷል።
የቻይና የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ቃል አቀባይ ጉኦ ጂያኩን፤ እገዳው “ውጥረቱን ከማባባስ እና ቀድሞውንም ደካማ የሆነውን የተኩስ አቁም ስምምነት ከመሸርሸር” ያለፈ ውጤት እንደማይኖረው አስጠንቅቀዋል።
“ይሄ አደገኛ እና ኃላፊነት የጎደለው ባሕሪ ነው” ሲሉ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ ተናግረዋል።
ቃል አቀባዩ አክለውም ቻይና ለኢራን አዲስ የአየር መከላከያ ስርዓት እያዘጋጀች ነው የሚሉ ዘገባዎች “ሙሉ በሙሉ ፈጠራ ናቸው” ሲሉ አስተባብለዋል።
ይህ ሪፖርት መውጣቱን ተከትሉ ፕሬዝዳንት ትራምፕ ቻይና ለኢራን ወታደራዊ እገዛ የምታደርግ ከሆነ በምርቶቿ ላይ የ50 በመቶ ታሪፍ እንደሚጥሉ ዝተዋል።
“አሜሪካ በቻይና ላይ ተጨማሪ ታሪፍ ለመጣል ይህንን እንደ ምክንያት የምትጠቀም ከሆነ፤ ቻይና በእርግጠኝነት ቆራጥ የአጸፋ እርምጃዎችን ትወስዳለች” ብለዋል።
BBC
