ሲቢኢ ካፒታል እና ንብ ባንክ ስትራቴጂያዊ ስምምነት ተፈራረሙ የኢትዮጵያ ፋይናንስ ተቋማት የሆኑት ሲቢኢ ካፒታል ኢንቨስትመንት ባንክ እና ንብ ኢንተርናሽናል ባንክ፣ ንብ ባንክን ለማስፋፋት የሚያስችል ስትራቴጂያዊ ስምምነት አደረጉ።
በስምምነቱ መሰረት፣ ንብ ባንክ የ ሲቢኢ ካፒታልን የኢንቨስትመንት ባንኪንግ አገልግሎት በመጠቀም፣ በፍጥነት እየተለወጠ ባለው የባንክ ገበያ ውስጥ ተወዳዳሪ ሆኖ ለመቀጠል የፋይናንስ አቅሙን እና የገበያ እውቀቱን ያጎለብታል ተብሏል።
የንብ ባንክ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ሄኖክ ከበደ ስምምነቱን “ለባለአክሲዮኖች የረጅም ጊዜ ጥቅም ለመፍጠር ወሳኝ እርምጃ ነው” ሲሉ ገልጸውታል።
የ CBE ካፒታል ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ ዘመዴነህ ነጋቱ በበኩላቸው፣ ስምምነቱ ንብ ባንክ “ብልህ ውሳኔዎችን እንዲያደርግ” ለመርዳት የገቡትን ቃል እንደሚያሳይ ተናግረዋል።
