ዝይን” ን ዳጎስ ብላ ስመለከት “ለካ ሰርቻለሁ፣ የሀገሬ ሥነ ጽሁፍ ውስጥ አለሁበት” የሚል ምስክርነት ለራሴ ተሰማኝ፣ ለመጀመሪያ ጊዜ!! አይጣበቅብኝ ፣ ለእብሪት አይዳርገኝ እንጂ አንዳንዴ ይሁን!
“ዝይን ” የሦስት ስራዎች ጥምር ናት፣ በፍቅር ሥም፣ ታለ እና ሐሰተኛው የአክሲዮኑ መስራቾች ናቸው።
ውበትና ጥራት ሲቲን ፋታ የነሳ ጉዳይ ሆኖ ይሄንን ውጤት አስገኝቷል። ሲቲን አመስግኑልኝማ!! ምስጋናው በሰፊው መድረክ ይቀጥላል። ደግሞምኮ “በፍቅር ሥም” ሲመረቅ ሁለት ለጣቂ ሥራዎች እንዳሉ ተለፍፎ፣ ለጥምረት ምርቃታቸው እንደምንገናኝ ቀጠሮ ተይዞ ነበር። እነሆ ያቺ የተቀጠበች ቀን ደርሳለችና እንገናኛለን!!
