የተመድ ዋና ፀሐፊ ቃል አቀባይ ስቴቨን ዱጃሪች፣ “አሜሪካ በሶሪያ የጣለቻቸውን ማዕቀቦች ማንሳቷ የሶሪያን ህዝብ የአኗኗር ዘይቤ ይቀይራል” ብለዋል።
የሶሪያ ቻምበር ኦፍ ኮሜርስ፣ “የማዕቀቡ መነሳት ኢኮኖሚስቶች ወደ ሀገራቸው እንዲመለሱ ያበረታታል” ሲል ገልጿል።
የሶሪያ የኢኮኖሚና ኢንዱስትሪ ሚኒስቴር፣ “የሶሪያ ኢኮኖሚ እንደ አዲስ እንዲያንሰራራ አስተዋጽኦ ያደርጋል” ባይ ናቸው።
ኳይት በበኩሏ፣ “ውሳኔውን እደግፋለሁ” ስትል ገልጻለች።
የኦማን ሱልጣን የማዕቀቡን መነሳት፣ “የሚበረታታ ነው” ብለውታል።
የመን ማዕቀቡ መነሳቱ ጥሩ እርምጃ መሆኑን በውጭ ጉዳይ ሚኒስቴሯ በኩል ገልጻለች።
የሊቢያ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “ለጉዳት የተጋለጠውን የሶሪያን ህዝብ ከችግር ለማውጣት የተወሰደ አወንታዊ እርምጃ ነው” ሲል ውሳኔውን ደግፏል።
የኳታር የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “አሜሪካ ማዕቀቡን ለማንሳት ያሳየችውን ድጋፍ እንደሚያደንቅ” ገልጿል።
የአሜሪካ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር፣ “በመካከለኛው ምሥራቅ ሰላምና ብልፅግናን ማዬት እንፈልጋለን” ሲል አስታውቋል።
