አንጋፋው የሙዚቃ ማናጀር አቶ አዲስ ገሠሠ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ

Date:

ዓለም አቀፍ እውቅና የነበራቸው የሙዚቃ ማናጀር አቶ አዲስ ገሠሠ ባደረባቸው ሕመም በ73 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል።

አቶ አዲስ በአሜሪካ ሀገር በሕክምና ሲረዱ ቆይተው ሰኔ 09 ቀን 2018 ዓ.ም ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸውን ቤተሰቦቻቸው ለኢቢሲ ገልጸዋል።

በዓለም አቀፍ የሙዚቃ መድረክ ላይ ስማቸው በጉልህ ከሚነሣ ኢትዮጵያውያን አንዱ የሆኑት አቶ አዲስ፣ የቦብ ማርሌን ቤተሰብ የሙዚቃ ሥራዎችን በአስተማማኝነት ከመምራት ባለፈ፣ ዚጊ ማርሌን ከኢትዮጵያው ዳሎል ባንድ ጋር በማጣመር “ኮንሺየስ ፓርቲ” በተሰኘው አልበም የግራሚ ሽልማት እንዲያገኙ ትልቅ ታሪክ ሠርተዋል።

በሀገር ውስጥ የሙዚቃ ዕድገትም የጎላ አሻራ ያሳረፉ ሲሆን፣ ከታዋቂ ድምፃውያን ስኬቶች ጀርባ የነበሩ ቁልፍ ሰው ነበሩ።

በማኅበራዊ ሕይወታቸው ቀልድ አዋቂ፣ ተጫዋች እና ሰው አክባሪ እንደነበሩ የሚነገርላቸው አቶ አዲስ፣ ባለትዳር እና የአንድ ወንድ እና የአንድ ሴት ልጅ አባት ነበሩ።

የአስከሬን ሽኝት እና የሥርዓተ ቀብር አፈጻጸም መርሐ-ግብር በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ቤተሰቦቻቸው አሳውቀዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የመረጃ ነጻነት አዋጅን በሙሉ ድምፅ አጸደቀ

በምክር ቤቱ የዲሞክራሲ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ አቶ እውነቱ...

በቬንዝዌላ በደረሰ የመሬት መንቀጥቀጥ የ32 ሰዎች ህይወት አልፏል

በቬንዙዌላ የአስቸኳይ ጊዜ አዋጅ የታወጀ ሲሆን 7.2 እና 7.5...

የጎንደር ዩኒቨርሲቲ “ሉሲ” ላገኟት ፕሮፌሰር የክብር ዶክትሬት ዲግሪ ሰጠ

የዩኒቨርሲቲው ሴኔት ሰኔ 16 ቀን 2018 ዓ.ም. ባካሄደው ስብሰባ፥...

የሳህለወርቅ ዘውዴ አዲሱ አለም አቀፍ ሹመት በተመድ ልዩ ተልእኮ ተሰጣቸው

የቀድሞዋ የኢትዮጵያ ፕሬዝደንት ወይዘሮ ሳህለወርቅ ዘውዴ በተመድ ዋና ፀሀፊ...