አየር መንገዱ ለቦርድ አባላቱ ሽኝት አደረገ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ የቀድሞ የአየር መንገዱ ቦርድ አባል ለነበሩት ክቡር የኢ.ፌ.ዲ. ሪ ፕሬዝደንት ታዬ አጽቀ ሥላሴ የሽኝት መርሐ ግብር አካሄደ።


በዚህ የሽኝት መርሀግብር ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ቦርድ ሰብሳቢ ክቡር ሌ/ጄኔራል ይልማ መርዳሳ፣ የቦርድ አባላት፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው እና የኢትዮጵያ አየር መንገድ ከፍተኛ የአመራር አባላት ተገኝተዋል።


በመርሀግብሩ ላይ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈፃሚ አቶ መስፍን ጣሰው ባስተላፉት መልዕክት አየር መንገዱ አህጉራዊ መሪነቱን እና አለም አቀፋዊ ተወዳዳሪነቱን አጠናክሮ እንዲቀጥል እንዲሁም እንደወትሮው ሁሉ የጥንካሬ የእድገት እና የአዳዲስ ዕመርታዎች ተምሳሌት ሆኖ እንዲዘልቅ ክቡር ፕሬዝደንት በቦርድ አባልነታቸው ላበረከቱት አስተዋፅዖ ምስጋና አቅርበዋል።


በተመሳሳይም አየር መንገዱን በቦርድ አባልነት ያገለገሉት የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር ሚኒስትር ዲኤታ ክብርት ወሮ ያስሚን ወሀብረቢ ሽኝት ተደርጎላቸዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...