አዲስ አበባ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ግዙፍ  ኮንፈረንስ ለማስተናገድ ተመረጠች

Date:

ኢትዮጵያና ኖርዌይ በመስከረም 2019 ዓ.ም በአይነቱ ትልቅ የሆነውን የኖርዲክ-አፍሪካ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ኮንፈረንስ በአዲስ አበባ ለማካሄድ ስምምነት ተፈራርመዋል።

ስምምነቱን የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ሚኒስትር ዴኤታ አቶ በርኦ ሀሰን እና በኢትዮጵያ የኖርዌይ አምባሳደር ስቲያን ክርስቲሰን በጋራ አጽድቀውታል። ይህ መድረክ በዘርፉ በየዓመቱ ከሚካሄዱ ዓለም አቀፍ መድረኮች አንዱና ቀዳሚው መሆኑ ተገልጿል።

ኖርዌይ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ትግበራ ከአውሮፓ ሀገራት ቀዳሚ መሆኗን የጠቀሱት አቶ በርኦ ሀሰን፣ ኮንፈረንሱ በአዲስ አበባ መካሄዱ በዘርፉ በተሰማሩ አመራሮች፣ ኢንቨስተሮችና ሙያተኞች መካከል ጠንካራ ትስስር ለመፍጠር ያስችላል ብለዋል።

በተጨማሪም የአውሮፓ ባለሀብቶች በኢትዮጵያ በስፋት እንዲሰማሩና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲፈጠር ትልቅ ዕድል እንደሚከፍት ሚኒስትር ዴኤታው አስረድተዋል።

አምባሳደር ስቲያን ክርስቲሰን በበኩላቸው፣ ኢትዮጵያ በኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ዙሪያ ያወጣቻቸውን ሕጎችና የጀመረቻቸውን ሥራዎች አድንቀዋል። ስምምነቱ የሁለቱን ሀገራት የቆየ ግንኙነት ወደ ንግድ ትብብር እንደሚያሳድገው የገለጹት አምባሳደሩ፣ ኖርዌይ በዘርፉ ያላትን ሰፊ ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል ዝግጁ መሆኗን አረጋግጠዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...