የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች ኢራንን ለመደብደብ ከአገራቸው ይነሱ እንደነበር ተናገሩ ።
ዩናይትድ ስቴትስ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ግድም ኢራንን ዳግም ስትደበድብ ቆይታ በድንገት ድብደባውን ባለፈው ዐርብ ጋብ አድርጋ አቋርጣለች ። በሁለት ሣምንቱ የኢራን ድብደባ እሥራኤል እንደ ከዚህ ቀደሙ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ተባብራ ድብደባ አልፈጸመችም ።
ምድሯን ለዩናይትድ ስቴትስ ጦር ጄቶች ክፍት በማድረጓ ለሚደርስባት ማናቸውም ጥቃት የአጸፌታ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መኾኗንም ይፋ አድርጋለች ።
የእሥራኤል ጠቅላይ ሚንሥትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ አገራቸው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በጋራ ኢራን ላይ ጦርነት ከከፈተችበት ጊዜ አንስቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ይመክራሉ ተብሏል ።
እሥራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ ከሔዝቦላህ ጋር የነበራቸውን ጦርነት በተመለከተ ከሊባኖስ ጋር ስለደረሱበት ስምምነትም ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል ።
