ኢራንን ለመምታት የዩናይትድ ስቴትስ ጄቶች ከምድሯ ይነሱ እንደነበር እሥራኤል ይፋ አደረገች

Date:

የእሥራኤል መከላከያ ሚንሥትር እሥራኤል ካትስ የዩናይትድ ስቴትስ የጦር ጄቶች ኢራንን ለመደብደብ ከአገራቸው ይነሱ እንደነበር ተናገሩ ።

ዩናይትድ ስቴትስ ላለፉት ሁለት ሳምንታት ግድም ኢራንን ዳግም ስትደበድብ ቆይታ በድንገት ድብደባውን ባለፈው ዐርብ ጋብ አድርጋ አቋርጣለች ። በሁለት ሣምንቱ የኢራን ድብደባ እሥራኤል እንደ ከዚህ ቀደሙ ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር ተባብራ ድብደባ አልፈጸመችም ።

ምድሯን ለዩናይትድ ስቴትስ ጦር ጄቶች ክፍት በማድረጓ ለሚደርስባት ማናቸውም ጥቃት የአጸፌታ ምላሽ ለመስጠት ዝግጁ መኾኗንም ይፋ አድርጋለች ።

የእሥራኤል ጠቅላይ ሚንሥትር ቤኒያሚን ኔታንያሁ አገራቸው ከዩናይትድ ስቴትስ ጋር በጋራ ኢራን ላይ ጦርነት ከከፈተችበት ጊዜ አንስቶ ለመጀመሪያ ጊዜ ከፕሬዚደንት ዶናልድ ትራምፕ ጋር ይመክራሉ ተብሏል ።

እሥራኤል እና ዩናይትድ ስቴትስ ከሔዝቦላህ ጋር የነበራቸውን ጦርነት በተመለከተ ከሊባኖስ ጋር ስለደረሱበት ስምምነትም ይነጋገራሉ ተብሎ ይጠበቃል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚሊዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ ቫይረስ ጋር ይኖራሉ

በኢትዮጵያ ከ10 ሚልዮን በላይ ሰዎች ከሄፓታይተስ ቢ እና ከ2...

የቶዮታ ኮሮላ መኪና በኤሌክትሪክ ሊመጣ ነዉ

የዓለማችን ግዙፍ የመኪና አምራች የሆነው ቶዮታ፤ እንደ ቴስላ እና...

በጋምቤላ ክልል በጀት ዓመት ከአምናው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነፃፀር ከ2 ቢሊዮን በላይ ጭማሪ አሳየ

 በጋምቤላ ክልል በበጀት አመቱ በተከናወነው የገቢ አሰባሰብ ዙሪያ የተሻለ...

አቶ ዓለማየሁ ጢሞቴዎስ የ10 ዓመት እስራት ተፈረደባቸው

‎‎የሲዳማ ክልል ፍትሕ ቢሮ እንዳስታወቀው የቀድሞ የሲዳማ ክልል ሰላም...