ኢራን ከአሜሪካ ጋር ተደርሶ የነበረውን ጊዜያዊ የሰላም ስምምነት ለመመለስ የተጀመረ ሂደት የለም

Date:

በባሕረ ሰላጤው የሚደረገውን ጦርነት የሚያስቆም ስምምነት ላይ እንዲደርሱ የሚደረገውን ጥረት በተመለከተ አሜሪካ እና ኢራን የገቡበት መፋጠጥ አሁንም መቀጠሉን የቴህራን ከፍተኛ ባለሥልጣን ለሮይተርስ ተናገሩ።

እንደ ባለሥልጣኑ ገለጻ፣ ባለፈው ሰኔ ላይ ተደርሶ የነበረው ጊዜያዊ የሰላም ስምምነት ለማስነሳት እና ለስምምነቱ ትግበራ የጊዜ ሰሌዳ ለማስቀመጥ የሚደረገው ጥረት ላይ የታየ መሻሻል የለም።

ማክሰኞ ዕለት በቀጠናው ይጓዙ የነበሩ መርከቦች ላይ የተፈጸመውን ጥቃት ተከትሎ፣ የአሜሪካ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በድጋሚ የኢራን መሪዎች ላይ ቁጣቸውን ገልጸዋል። ይህ ክስተትም ሁለቱ አገራት ስምምነት ላይ ይደርሳሉ የሚለውን ተስፋ ይበልጥ አደጋ ውስጥ ጥሎታል።

ሰኔ ላይ የተፈረመው ስምምነት፣ “በሁሉም ግንባሮች የሚካሄዱ ወታደራዊ እንቅስቃሴዎች ወዲያውኑ እና በዘላቂነት እንዲቆሙ” የሚያደርግ ነበር። ይሁን እንጂ ስምምነቱ ከተፈረመ ከሳምንታት በኋላ ሁለቱ አገራት አንዳቸው በሌላቸው ላይ ጥቃት መፈጸመው ጀምረዋል።

ይህንን ተከትሎም ፕሬዝዳንት ትራምፕ ስምምነቱ “እንዳበቃ” የተናገሩ ሲሆን የኢራን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴርም ስምምነቱ “መታገዱን” ገልጿል።

አሜሪካ፣ በስምምነቱ መሠረት ኢራን የሆርሙዝ ወሽመጥን አልከፈትም በማለት ትከስሳለች። ቴህራን በበኩሏ፣ ዋሽንግተን የኢራን ወደቦች ላይ የተጣለው የጉዞ እገዳን ማንሳት እና የታገዱ ሀብቶችን እንደማስለቀቅ ያሉ እርምጃዎችን አለመውሰዷን ትናገራለች።

የዜና ወኪሉ ሮይተርስ ያነጋገራቸው ኢራን ምንጭ፣ “በአሸማጋዮዎች ውይይት እየተደረገበት ያለው አንዱ ጉዳይ የአሜሪካ ወደ ጊዜያዊ ስምምነቱ መመለስ እና የገባቻቸውን ቃሎች የምስፈጽምበት የጊዜ ሰሌዳን ማስቀመጥ” እንደሆነ ገልጸዋል።

ነገር ግን “በዚህ ጉዳይ ላይ ምንም አይነት መሻሻል የለም” ሲሉ ለዜና ምንጩ ተናግረዋል።

ፕሬዝዳንት ትራምፕ ረቡዕ ዕለት በትሩዝ ሶሻል ማኅበራዊ ሚዲያ ገጻቸው ባሰፈሩት ጽሑፍ፣ አሜሪካ በሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ “ሙሉ ቁጥጥር” ተናግረዋል።

ወደ ኢራን ወደቦች የሚደረግ ጉዞ ላይ የተጣለው እግድም እንዳለ በመጥቀስ “ኢራን ልታደርግ የምትችለው ምንም ነገር የለም” ብለዋል።

ኢራን ሆርሙዝ ወሽመጥን ለማስተዳደር ያቋቋመችው የፋርስ ባሕረ ሰላጤ ወሽመጥ ባለሥልጣን ግን የትራምፕን አስተያየት አጣጥሏል። “ሆርሙዝ ወሽመጥ ላይ እገዳ የለም የሚለው የአሜሪካ ባለሥልጣናት ገለጻ እና ተደጋጋሚ ልጥፍ እውነታውን አይቀይረውም” ብሏል።

“ሆርሙዝ ወሽመጥ እንደተዘጋ ይቆያል፣ የኢራን ቅድመ ሁኔታዎች ተቀባይነት እስካላገኙ ድረስ አይከፈትም” ሲልም አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ይህንዓለም አቅናው የአማራ ባንክ ዋና ሥራ አስፈፃሚ ሆኑ

በኢትዮጵያ በፍጥነት እያደጉ ከሚገኙ እና ከፍተኛ የባለአክስዮኖች ቁጥር ካላቸው...

ማዕቀቦች የኢራንን የኒውክሌር መርሃ-ግብር ቢያደናቅፉም መንግስቱን ሊጥሉ እንደማይችሉ ተገለጸ

ማዕቀቦች የኢራንን ወታደራዊ እና የኒውክሌር እንቅስቃሴዎች አስቸጋሪና ውድ እንዲሆኑ...

የአፍሪካ ሀገራት አዲስ የኢንቨስትመንት ፈንድ ይፋ አደረጉ

በአፍሪካ ሀገራት ላይ የተደቀነውን ከፍተኛ የብድር ጫና ለማቃለል እና...

ዶናልድ ትራምፕ “በቅርቡ” ሆርሙዝ የአሜሪካ ግዛት አካል እንደሚሆን ተናገሩ

ከኢራን ጋር ያለው ግጭት እየተባባሰ ባለበት በአሁኑ ሰዓት የአሜሪካው...