“ኢራን የከፋ ነገር ይጠብቃታል”ትራምፕ

Date:


ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ የአሜሪካ ፍላጎቶች ካልተሟሉ የከፋ ነገር ይገጥማታል ሲሉ ዛቱ።

ኢራንና አሜሪካ ወደ ድርድሩ መድረክ ከስምንት ወራት በኋላ ቢመለሱም ትራምፕ ወታደራዊ እርምጃን ግምት ውስጥ እያስገቡ ነው።

ከኑክሌር ማብላላት እስከ ሚሳኤል መርሃ ግብር ድረስ ቴህራን የዋሽንግተንን ፍላጎት እንድታሟላ ሪፐብሊካኑ ፍላጎታቸው ሆኗል።

በሌላ በኩል አያቶላዉያኑ ከብሄራዊ ጥቅማችን በተወሰነ መጠንም ቢሆን ዝንፍ አንልም በሚል እየሞገቱ ይገኛል።

ስምምነት ላይ ካልተደረሰ አደገኛ እርምጃ በኢራን ላይ እንደሚወሰድ ትራምፕ ይግለፁ እንጂ በኢራን በኩል ያለው ወታደራዊ ዝግጅትም ስጋት ሆኖባቸዋል።

“ወይ ከስምምነት ላይ እንደርሳለን፤ካልሆነ ግን የሆነ እጅግ ብርቱ ነገር ይኖረናል”ብለዋል ትራምፕ።

ይህ አስተያየት የተሰማው የኢራን የደህንነት ሀላፊ አሊ ላሪጃኒ ከዖማኑ ሱክጣን ቢን ታሪቅ አል-ሰይድ ጋር በድርድሩ ውጤት ላይ እየተመካከሩ ባሉበት ሰዓት ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...