ኢትዮጵያ በክትባት ተደራሽ ካልሆኑ እና ጀምረው ከሚያቋርጡ ሀገራት 4ተኛ ሆነች

Date:

ሀገሪቱ እ.ኤ.አ በ2021 ወደ 1 ነጥብ 4 ሚሊየን ህጻናት ክትባት ያልወሰዱ እና ጀምረው ያቋረጡባት ቢሆንም በ2024 ግን ወደ 768 ሺህ ዝቅ ማለቱን በጤና ሚኒስቴር የብሔራዊ የክትባት ፕግራም የዴስክ አማካሪ ወ/ሮ ጸጋነሽ ገድሉ ገልጸዋል፡፡

ይሁንና ይሄ ቁጥር ቀላል የማይባል በመሆኑ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስራ መስራት እንደሚያስፈልግ አንስተዋል።

በጤና ባለሙያዎች እና በአስከታቢዎች መካከል ያለው ተግባቦት በቂ አለመሆን፣ እናቶች ስለ ክትባቱ ጥቅም አስፈለጊውን ግንዛቤ አለማግኘታቸው፣ ክትባቱ ስላለው የጎንዮሽ ጉዳት እና በቀጣይ ምን ማድረግ እንዳለባቸው አለማወቅ ህጻናቱ ክትባት ጀምረው የሚያቋርጡባቸው መንስኤዎች መሆናቸውን ጠቁመዋል።

በተጨማሪም ፍትሃዊ የክትባት ሽፋን አለመኖሩ፣ የሰላም እጦት እና ተፈጥሯዊ አደጋዎች ፈተናዎች እንደሆኑም ገልፀዋል።

ወላጆች ከአምስት አመት በታች ያሉ ህጻናትን በተገቢው ወደ ጤና ተቋማት በመውሰድ እንዲያስከትቡም አሳስበዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...