በመከላከያ ሚኒስትሯ አይሻ መሀመድ የተመራ ልዑክ በጀርመን በርሊን በተካሄደው የተመድ የሰላም ማስከበር የሚኒስትሮች ስብሰባ ላይ ተሳትፏል።
ሚኒስትሯ በጉባኤው ላይ ባደረጉት ንግግር ኢትዮጵያ በዓለም አቀፍ የሰላም አስከባሪዎች ማሰልጠኛ ኢንስቲትዩት ውስጥ ስልጠና መስጠቷን ለመቀጠል ቁርጠኛ ነች ብለዋል፡፡
በተለይም ተቋሙ በሴት ሰላም አስከባሪዎች ስልጠና ላይ በትኩረት ለመሥራት ማቀዱን ተናግረዋል ሲል መከላከያ ሠራዊት አስታውቋል።
