ኢትዮጵያ የባህር ወደብ የሌላት በመሆኑ የሎጀስቲክ ዘርፍ ላይ ከፍተኛ ጫና መፍጠሩ ተጠቆመ

Date:

የኢትዮጵያ የዕቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማህበር እና የብሪታኒያ ዓለም አቀፍ የጭነት አስተላላፊዎች ማህበር በጋራ ለመስራት የሚያስችላቸውን የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል ፡፡

በስነስርዓቱ ላይ እንደተገለጸው በኢትዮጵያ የሎጀስቲክ ዘርፍ ያለበት ደረጃ እጅግ በጣም ዝቅተኛ ኋላቀር ነው ፡፡
ለዚህ እንደምክንያት የተገለጸው ደግሞ ኢትዮጵያ የራሷ የባህር ወደብ የሌላት በመሆኑ በዘርፉ ላይ ከፍተኛ ጫና ሊፈጥር ችሏል ፡፡

አቶ ዳዊት ውብሸት የኢትዮጵያ ዕቃ አስተላላፊዎችና የመርከብ ወኪሎች ማህበር ፕሬዝዳንት እንዳስታወቁት ኢትዮጵያ በዘርፉ በዘላቂነት ተጠቃሚ እንድትሆን የባህር በር ጉዳይ ውሳኔ ማግኘት አለበት ፡፡

ሁለቱ አቻ ማህበራትን የኢትዮጵያ የሎጀስቲክ ዘርፍ ዘመናዊና ተወዳዳሪ ለማድረግ በአቅም ግንባታ ፣የልምድ ልውውጥና ተያያዥ ስራዎችን በጋራ ለመስራት ስምምነት መፈጸማቸው ተናግረዋል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...