ኢትዮጵያ የአፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣናን ትግበራ እንደምትጀምር ተሰማ

Date:

ኢትዮጵያ በሚቀጥለው ሳምንት ምርቶቿን ከቀረጥ ነጻ በሆነ ሥርዓት ወደ አፍሪካ አህጉራዊ ነጻ የንግድ ቀጣና (AfCFTA) ማዕቀፍ አባል አገራት መላክ እንደምትጀምር የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስቴር አስታወቀ።

የንግድና ቀጣናዊ ትስስር ሚኒስትር ካሳሁን ጎፌ ለብዙኃን መገናኛዎች በሰጡት መግለጫ ፤ ኢትዮጵያ መስከረም 29 ቀን የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የሸቀጦች ንግድ ትግበራን በይፋ ታስጀምራለች።

በሥነ ሥርዓቱ ላይ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጣና ዋና ስራ አስፈጻሚን ጨምሮ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እንደሚገኙም ተጠቁሟል።

ከዚህ ቀደም ኢትዮጵያ ወደ ኬኒያ የምትልከው እንደ በቆሎ እና ቦለቄ ያሉ ሸቀጦች 15 በመቶ ቀረጥ ይጣልባቸው እንደነበር ነው። ነገር ግን፣ የመጀመሪያውን ጭነት ካስጀመረች በኋላ፣ ኢትዮጵያ ወደ ኬኒያ የምትልከው ሸቀጥ ከቀረጥ ነጻ እንደሚሆን ተናግረዋል።

CapitalNews

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...