ከፈንታሌ ወረዳ ስድስት ሰዎች በኮሌራ በሽታ ህይወታቸው አለፈ

Date:

በኦሮሚያ ክልል በፈንታሌ ወረዳ በመሬት በተከሰተው መንቀጥቀጥ የተፈናቀሉ ስድስት ሰዎች በንፁህ ውሃ እጦት ምክንያት በተከሰተ የኮሌራ በሽታ መሞታቸውን የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ አሰቦት ለአዲስ ስታንዳርድ ተናገሩ።

ኃላፊው ተፈናቃዮቹ ንጹህ የመጠጥ ውሃ በማጣታቸው የዝናብ ውሃን ለመጠጥነት እየተጠቀሙ መሆኑን በመግለጽ፤ “በርካታ ሰዎች በኮሌራ በሽታ ተይዘው ስድስት ሰዎች ሞተዋል” ሲሉ ተናግረዋል።

የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪና የግብርና ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መሀመድ፤ “ከዚህ ቀደም እርዳታ በቡሳ ጎኖፋ እና በእርዳታ ድርጅቶች በኩል ይሰጥ ነበር” ሲሉ ገልጸው፤ አሁን ግን ሲደረግልን የነበረው እርዳታ “ሙሉ ለሙሉ ተቋርጧል” ብለዋል።

በተመሳሳይ መልኩ በ አፋር ክልል እንደ ዱለቻ እና አዋሽ ፋንታሌ ካሉ ወረዳዎች ተፈናቅለው በመጠለያ ካምፖች ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎች በእርዳታ እጦት እየተቸገሩ መሆኑን ለአዲስ ስታንዳርድ አስረድተዋል።

ከአፋር ክልል ዱለቻ ወረዳ መፈናቀላቸውን የተናገሩት መሀመድደወል ኦስማን፤ “የሰብዓዊ እርዳታ ቢያንስ ላለፉት ሶስት ወራት ተቋርጧል” ሲሉ ጠቅሰው፤ ተፈናቃዮቹ በምግብ እና የመጠጥ ውሃ እጦት ችግር ውስጥ መሆናቸውን አስረድተዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...