ከ10 ህጻናት ስድስቱ ለነርቭ ዘንግ ችግር ይጋለጣሉ

Date:

በኢትዮጵያ የነርቭ ዘንግ ችግር የሌለባቸውን ልጆች መውለድ የሚችሉት 29 በመቶ ሴቶች ብቻ መሆናቸው ተገልጿል።

ከ10 እናቶች መካከል 6ቱ የነርቭ ችግር ያለባቸውን ህፃናት ሊወልዱ እንደሚችሉ የኢትዮጵያ ሕብረተሰብ ጤና ኢንስቲቲዩት አጥኚ ዶክተር ማስረሻ ተሰማ ገልፀዋል።

የበሽታው ምክንያትም ምግብን በጠቃሚ ንጥረ ነገሮች አለማበልፀግ መሆኑ ተመላክቷል። ይህ የጤና ችግር ዜጎች የተስተካከለ የሰውነት ክፍል እንዳይኖራቸው ሊያደርግ እንደሚችል ተገልጿል።

የነርቭዘንግ ችግር ከተሰኘው የበሽታ አይነት ጋር በተያያዘ በዓመት ከ30 ሺሕ በላይ ህፃናት እንደሚወለዱ የሆፕ ኤስ ቢ ኤች ስራ አስኪያጅ ቤዛ በሻህ ገልፀዋል።

በበርካታ ሆስፒታሎች ህክምናው አለመኖሩ እና ዜጎች ቅድመ መከላከል ላይ ያላቸው ግንዛቤ አነስተኛ መሆን የበርካታ ህፃናት ህይወት እንደሚጠፋ ምክንያት መሆኑን ስራ አስኪያጇ ተናግረዋል።

የበሽታው ተጠቂ የሆኑ ግለሰቦች ሽንት መቆጣጠር የማይችሉ እና በራሳቸው መንቀሳቀስ የሚያዳግታቸው እንደሆኑም ተገልጿል።

(ሀገሬ ቴቪ)፤

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...