ከ3ሺ በላይ ሰዎች ተገድለዋል

Date:


ሂዝቦላህ የተኩስ አቁም ስምምነት ውድቅ ማድረጉ ሰገለጽ፥ የእስራኤል ከባድ ጥቃቶች ተፋፍመው መቀጠላቸው ተነገረ።

የሊባኖሱ ሄዝቦላህ በእስራኤል እና በሊባኖስ የተደረሰውን የተኩስ አቁም ስምምነት ውድቅ ሲያደርግ የእስራኤል ከባድ ጥቃቶች ተፋፍመው መቀጠላቸው ተነግሯል።

በኢራን የሚደገፈው የሄዝቦላህ ዋና አዛዥ ናኢም ቃሲም በሰጡት መግለጫ፥ ” ድርድሩ ለሊባኖስ ከንቱ እና አዋራጅ” ነበር ሲሉ ተችተዋል።

ለይስሙላ የተደረገ ሲሉም  የተኩስ አቁም ስምምነቱን ውድቅ አድርገውታል።

እስራኤል በሊባኖስ ጥቃትና ድብደባዋን እስከቀጠለች ድረስ ሰሜናዊ እስራኤል የተፋላሚዎች ኢላማ ትሆናለች ሲሉም አስጠንቅቀዋል ዋና አዛዡ ቃሲም።

የኢራን እስላማዊ አብዮታዊ ዘብ (IRGC) እስራኤል ከሊባኖስ ግዛት እስክትወጣ ድረስ “በአካባቢው ሰላም አይኖርም” ሲል በቴህራን እና በዋሽንግተን መካከል የተደረገው ስምምነት በዋናነት በሊባኖስ ያለውን ግጭት ማቆምን ያካትታል ሲል አሳስቧል።

ይህ በእንዲህ እንዳለ በአሜሪካ አደራዳሪነት በሊባኖስ እና በእስራኤል ባለስልጣናት መካከል በዋሽንግተን ዲሲ የተደረሰው የተኩስ አቁም በቀጠለበት፥ እስራኤል ከባድ ጥቃቶችን በመላው ሊባኖስ አጠናክራ መቀጠሏ ተነግሯል።

ከመጋቢት 2 ጀምሮ እስራኤል በሊባኖስ ላይ ባደረሰችው ጥቃት ቢያንስ 3ሺ 526 ሰዎች ሲገደሉ፥ 10ሺ 733 ቆስለዋል ሲል የሀገሪቱ የጤና ጥበቃ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ዘገባው የአልጀዚራና ቢቢሲ ነው።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

በ2026 የዓለም ዋንጫ ላይ ለተለያዩ ብሔራዊ ቡድኖች የሚጫወቱ ወንድማማቾች

የ2026 የፊፋ የዓለም ዋንጫ ከመላው ዓለም የተውጣጡ ምርጥ ተጫዋቾችን...

ኢንፊኒቲ ለቤትና ለመኪና መግዣ ብድር እየሰጠ እንደሚገኝ አስታወቀ

ኢንፊኒቲ ኃላፊነቱ የተወሠነ መሠረታዊ የቁጠባ እና ብድር ኀብረት ሥራ...

የአዲሱ የወንጀል ህግ ስነ-ስርዓት የእርማት ስራዎች ሳይጠናቀቁ በሥራ ላይ እየዋለ ነው

የኢፌዴሪ የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ላለፉት 64 ዓመታት...

ናይጄሪያው ዩናይትድ ካፒታል በኢትዮጵያ የመጀመሪያውን የውጭ ኢንቨስትመንት ባንክ ፈቃድ አገኘ

​የኢትዮጵያ ካፒታል ገበያ ባለሥልጣን በሀገሪቱ የካፒታል ገበያ ታሪክ ለመጀመሪያ...