ካቻ ዲጂታል ፋይናንሻል ሰርቪስ ከኢትዮጵያ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚንስቴር ጋር በመተባበር ለአሽከርካሪዎች ከዘመኑ እኩል የሚራመድ የዲጂታል ነዳጅ ከፍያ አማራጭ በዛሬው እለት አስጀምሯል
ካቻ ዲጂታል ፋይናንሻል ሰርቪስ ከኢትዮጵያ ትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚንስቴር ጋር በመተባበር አበሩስ ህንፃ ጎን በሚገኘው ኦላ የነዳጅ ጣቢያ የትራንስፖርት እና ሎጀስቲክስ ሚኒስቴር መስሪያ ቤት ባለድርሻ አካላት፣ የፋይናንስ ተቋም ባለስልጣኖች፣ የውጭ ምንዛሬ ቢሮ ሀላፊዎች፣ የአጋር ድርጅት ሀላፊዎች የማስጀመሪያ መርሀገብር ያካሄደ ሲሆን አገልግሎቱ በተወሰኑ ማደያዎች እንደሚሰጥና በቀጣይ በሁሉም ማደያዎች እንደሚሰጥ ተገልጿል።
አገልግሎቱን በካቻ የሞባይል አፕ ማግኘት እንደሚቻል የተገለፀ ሲሆን የመኪና ኢንሹራንስ አገልግሎቶችንም በካቻ መክፈል እንደሚቻል ተነግሯል።
