ህንድ የፓኪስታን ዲፕሎማት በ24 ሰዓታት ውስጥ ለቀው እንዲወጡ አዘዘች።
አንድ ስማቸው ያልተጠቀሰ በኒው ደልሂ የፓኪስታን ኤምባሲ ዲፕሎማት’’ ያልተገባ ነገር አደርጓል’’ በሚል የህንድ የውስጥ ጉዳዮች ሚኒስቴር ከሷል።
ከአንድ የኤምባሲ ሰራተኛ የማይጠበቅ በሚል ክሱን ለማጠናከርም ሞክሯል ሚኒስቴሩ።
ያልተገባ ነገር አድርጓል ከማለት የተሻገረ ተጨባጭ ሀሳብ ከደልሂ በኩል ይህ ዜና እስከተጠናቀረበት ሰዓት ድረስ ይፋ አልሆነም።
ፓኪስታን እና ህንድ አምስተኛውን ጦርነታቸውን ሊያደርጉ ነው በሚል ቀጠናው ስጋት ውስጥ ባለበት ሰዓት ባለስልጣኑን ማባረር ተጨማሪ ቀውስ ሊፈጥር ይችላል ተብሏል።
የህንዱ ጠቅላይ ሚኒስትር ናሬንድራ ሞዲ አሸባሪዎችን እና ስጋት የደቀኑብንን ሁሉ መምታታችንን እንቀጥላለን ካሉ በኋላ ነው የዲፕሎማቱ ይውጣ መግለጫ ይፋ የሆነው።
በሌላ በኩል ፓኪስታን ተኩስ አቁሙን ለማክበር ቁርጠኛ መሆኗን በመግለጽ ከኒው ድለሂ በኩል ጥቃት ከተሰነዘረብኝ ግን አደገኛውን አጸፋ እሰጣለሁ በሚልም ዝታለች።
የኒው ደልሂን ውሳኔ እስላማባድ ከጦርነቱ ጋር ልታገናኘው ትችላለች የሚል ስጋትም ተደቅኗል።
የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ በሁለቱ አገራት መካከል ተቀስቅሶ የነበረውን ግጭት በተኩስ አቁም ለጊዜውም ቢሆን ማስቆማቸው የሚዘነጋ አይደለም።
