በኢትዮ ኤርትራ ጉዳይ በተለይም የባህር በር ጉዳይ በቅንነት ኢትዮጵያ ይገባታል ብዬ የማምንበት ነው።
ከዚህ ቀደም እንደጻፍኩት የኢትዮጵያ ህዝብ የኤርትራ መገንጠልን ሰማ እንጂ የወሰነው ጉዳይ የለም። መለስና ኢሳያስ ናቸው ዋና ወሳኞቹ።
ይኼ የሽርክና ውሳኔም ለትንሿ አገር ኤርትራ ወደ 1000 ኪ.ሜ የሚጠጋ የባህር በር ሰጥቶ ብዙ ህዝብ ያላትን ኢትዮጵያን ከባህሩም ከወደቡም የገፋ ኢ-ፍትሃዊ ውሳኔ ነው።
መለስ የመራው የሽግግር መንግስት መገንጠሉን እሽ ይደግፍ እንበል ግን የኢትዮጵያን ታሪካዊ ወደብ አሳልፎ የሰጠበት እብደት ግን የሚያስተዛዝብ ነው።
በዛሬው ዜና መንግስት የኤርትራን የአገርነት ዕውቅና ሊነፍግ ዳርዳር እያለ ይመስላል። ይኼ ለኤርትራ ጥሩ አይመስለኝም። ስለዚህ በዚህም በዚያም በኩል ከመፎከር ሰከን ብሎ ያለ መገፋፋት ኢትዮጵያ የባህር በር የምታገኝበትን መንገዶ ኢሱ ጭሱ ቢያስብበት ጥሩ ነው።
ዳንኤል ተፈራ
