ወደ ብልጥግናም ወደ ተቃዋሚው ፍላጎት ሳትወስዱ አንብቡኝ

Date:

በኢትዮ ኤርትራ ጉዳይ በተለይም የባህር በር ጉዳይ በቅንነት ኢትዮጵያ ይገባታል ብዬ የማምንበት ነው።

ከዚህ ቀደም እንደጻፍኩት የኢትዮጵያ ህዝብ የኤርትራ መገንጠልን ሰማ እንጂ የወሰነው ጉዳይ የለም። መለስና ኢሳያስ ናቸው ዋና ወሳኞቹ።

ይኼ የሽርክና ውሳኔም ለትንሿ አገር ኤርትራ ወደ 1000 ኪ.ሜ የሚጠጋ የባህር በር ሰጥቶ ብዙ ህዝብ ያላትን ኢትዮጵያን ከባህሩም ከወደቡም የገፋ ኢ-ፍትሃዊ ውሳኔ ነው።

መለስ የመራው የሽግግር መንግስት መገንጠሉን እሽ ይደግፍ እንበል ግን የኢትዮጵያን ታሪካዊ ወደብ አሳልፎ የሰጠበት እብደት ግን የሚያስተዛዝብ ነው።

በዛሬው ዜና መንግስት የኤርትራን የአገርነት ዕውቅና ሊነፍግ ዳርዳር እያለ ይመስላል። ይኼ ለኤርትራ ጥሩ አይመስለኝም። ስለዚህ በዚህም በዚያም በኩል ከመፎከር ሰከን ብሎ ያለ መገፋፋት ኢትዮጵያ የባህር በር የምታገኝበትን መንገዶ ኢሱ ጭሱ ቢያስብበት ጥሩ ነው።

ዳንኤል ተፈራ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...