ዓለምን ያስጨነቀው የኢራን ፈንጂ

Date:

ኢራን በዓለም አቀፍ የነዳጅ ንግድ ውስጥ ቁልፍ መተላለፊያ በሆነው የሆርሙዝ ሰርጥ ላይ የባህር ላይ ፈንጂዎችን መጥመድ መጀመሯ በቀጠናው ያለውን ወታደራዊ ውጥረት ወደ አዲስ ምዕራፍ አሸጋግሮታል።

የአሜሪካ የስለላ ተቋማትና የሲኤንኤን ዘገባዎች እንደሚያመለክቱት፣ የኢራን አብዮታዊ ዘብ (IRGC) ትናንሽና ፈጣን ጀልባዎችን በመጠቀም በመርከብ መተላለፊያ መስመሮች ላይ በአስር የሚቆጠሩ ፈንጂዎችን አሰማርቷል።

ይህ እርምጃ ቀጠናው “የሞት ሸለቆ” የሚል ስያሜ እንዲሰጠው ያደረገ ሲሆን፣ ከፈንጂዎቹ በተጨማሪ በፈንጂ የተሞሉ አጥፍቶ ጠፊ ጀልባዎችና የባህር ዳርቻ ሚሳኤሎች መሰማራታቸው ስጋቱን አባብሶታል።

የዚህ ወታደራዊ እንቅስቃሴ ተፅዕኖ በዓለም አቀፍ ኢኮኖሚ ላይ ወዲያውኑ ታይቷል። የነዳጅ ዋጋ በከፍተኛ ሁኔታ የጨመረ ሲሆን፣ ታዋቂ የባህር ላይ መድን ሰጪ ድርጅቶች ለአካባቢው የሚሰጡትን የ”ጦርነት ስጋት” ሽፋን ሰርዘዋል።

በአሁኑ ወቅት ከ150 በላይ የነዳጅና የጋዝ ጫኝ መርከቦች በባህረ ሰላጤው መግቢያና መውጫ ላይ ቆመው ቀጣዩን ሁኔታ በመጠባበቅ ላይ ይገኛሉ።

አሜሪካ የነዳጅ ጫኝ መርከቦችን በወታደራዊ ኃይል ታጅበው እንዲጓዙ የማድረግ አማራጭን እያጠናች ቢሆንም፣ እስካሁን ይፋዊ ጥበቃ አለመጀመሩ የዓለምን የንግድ ፍሰት በከፍተኛ ስጋት ውስጥ ጥሎታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ካናዳ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል"...

የክቡር ዶክተር ጋሽ መሐሙድ አዲስ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነዉ

ታዋቂው ድምፃዊ ክቡር ዶክተር አርቲስት መሐሙድ አሕመድ «ለታሪክ» የተሰኘውንና...

ሜታ ‘ፌስቡክ እና ኢንስታግራም በቀረበባቸው ክስ 18 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ

ግዙፉ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያ ሜታ በፌስቡክ እና በኢንስታግራም ምክንያት...