ዘመን ገበያ አዲስ አመት ኤግዚቢሽን እና ባዛር በታሜሶል ኮሚዩኒኬሽን አዘጋጅነት ሊካሄድ ነው

Date:

የ2017 ዓ.ም የዘመን ገበያ አዲስ አመት ኤግዚቢሽንና ባዛርን ለማዘጋጀት ታሜሶል ኮሚዩኒኬሽን በ92.8 ሚሊዮን ብር ጨረታ ማሸነፉ ተገልጿል ።

ይህ ትልቅ ዝግጅት “ዘመን ገበያ አዲስ ነገር በአዲስ ዓመት ኤክስፖ 2018” በሚል መሪ ቃል በአዲስ አበባ ኤግዚቢሽን ማዕከል ከነሐሴ 17 እስከ ጳጉሜ 5 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይካሄዳል።

ዝግጅቱ ከኢትዮ ቴሌኮም ጋር በሽርክና የሚዘጋጅ ሲሆን፣ የቴሌብር ሱፐርአፕን ለህብረተሰቡ በስፋት ለማስተዋወቅ ታስቦበት እንደሆነም ታውቋል።

በኤግዚቢሽኑ ላይ ከ300 በላይ የአገር ውስጥ ነጋዴዎችና አገልግሎት ሰጪዎች የሚሳተፉ ሲሆን፣ ከህንድ፣ ከቱርክ፣ ከቻይና፣ ከተባበሩት አረብ ኤምሬቶች እና ከሌሎች ሀገራት የመጡ ኤግዚቢተሮችም እንደሚገኙበት ተገልጿል።

የኤግዚቢሽኑ ተሳታፊዎች ለህብረተሰቡ ሰፊ ምርጫ የሚያቀርቡ ሲሆን፣ ከትምህርት ቁሳቁስ፣ የቤት እቃዎች እና ቴክኖሎጂን ጨምሮ የተለያዩ የፍጆታ ዕቃዎች ይቀርባሉ ተብሏል።

ከዚህም በተጨማሪ፣ ዋና ዋና ባንኮች እና የፋይናንስ ተቋማት የሚገኙበት ልዩ “ፋይናንስ መንደር” የሚል ቦታ መዘጋጀቱ በዝግጅቱ ላይ ተጨማሪ ለውጥ ያመጣል ተብሎ ይጠበቃል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...