የሆረ ፊንፊኔ ኢሬቻ በዓል ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በስኬት መጠናቀቁን የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ገልጿል፡፡
የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ከሌሎች የፀጥታና ደኅንነት ተቋማት ጋር በመቀናጀት በቴክኖሎጂ የታገዘ 24/7 የተጠናከረ ጥበቃ ማድረጉን በመግለፅ፤ የሆረ ፊንፊኔ በዓል ባህላዊ እሴቱን ጠብቆ በስኬት እንዲጠናቀቅ ኃላፊነቱን መወጣቱን አስታውቋል፡፡
ለፀጥታ መዋቅሩ አስፈላጊውን ትብብር ላደረጉት የበዓሉ ታዳሚዎችም ፌደራል ፖሊስ ምስጋና አቅርቧል።
