የመከላከያ ሠራዊት አባላት በእሥራት ተቀጡ

Date:


በህገ ወጥ የሠዎች ዝውውር ተሠማርተዋል የተባሉ አንድ ከፍተኛ የአገር መከላከያ ሠራዊት አዛዥን ጨምሮ ሁለት የሠራዊቱ አባላት በ8 ዓመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት ተቀጡ፡፡


አባላቱ ቅጣቱ የተላለፈባቸው ትናንት በአርባምንጭ ከተማ በተሰየመው የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ባሳለፈው የፍርድ ውሳኔ ነው ፡፡
ቅጣቱ የተወሰነው በሠራዊቱ የደቡብ ዕዝ 202ኛ ኮር 1ኛ ሬጅመንት አዛዥ ሻምበል መብራቱ ታዴ እና በሬጅመንቱ የኦራል አሽከርካሪ በሆነው ወታደር ጌታቸው ክብረት በተባሉት ላይ ነው ፡፡


አዛዡ እና የሰራዊቱ አባል ቅጣቱ የተወሰነባቸው ህዳር 16 2016 ዓ.ም 52 ኤርትራዊያንን በሠራዊቱ የኦራል ተሽከርካሪ በመጫን ወደ ኬኒያ በማሻገር ላይ እንዳሉ በመያዛቸው መሆኑን የጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት አቶ ሽመልስ ጮራ ለዶቼ ቬለ ገልጸዋል ፡፡


የፌደራል ፍትህ ሚኒስቴር ዐቃቤ ህግ ክሱ በውክልና በጋሞ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት እንዲታይለት ባቀረበው የክስ መዝገብ መሰረት የተከሳሾቹን ጉዳይ ሲመለከት መቆየቱን የጠቀሱት ፕሬዝዳንቱ “ ተከሳሾቹ የሰዎች ዝውውር ወንጀሉን የፈጸሙት ለግዳጅ የተሠጣቸውና የሠሌዳ ቁጥሩ መከ ኮድ 2-2347 የሆነ ኦራል ተሽከርካሪን በመጠቀም ነው ፡፡

ሰዎቹን በመጓጓዝ ላይ እንዳሉ የተያዙትም በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አሌ ዞን ቀርቀርቴ በተባለ የገጠር ቀበሌ ውስጥ ነው ፡፡ ተከሳሾቹ በፎቶ ፣ በሰነድ አና በሰው ምስክር የቀረበባቸውን ክስ ሊያሰተባብሉ አልቻሉም ፡፡

የሐዋሳው ወኪላችን ሸዋንግዛው ወጋየሁ የዞኑን ከፍተኛ ፍርድ ቤት ዳኛ ጠቅሶ እንደዘገበው ፍርድ ቤቱ እያንዳንዳቸው በ8 ዓመት ከ5 ወር ፅኑ እስራት እና እንዲሁም በ10,000 ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ ተወስኗል ፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከ989 ሚሊዮን ብር በላይ የኮንትሮባንድ እቃዎች በቁጥጥር ስር ዋሉ

የጉምሩክ ኮሚሽን ከግንቦት 27 እስከ ሰኔ 3 ቀን 2018...

“እኔ እስካለሁ ድረስ ኢራን የኑክሌር መሣሪያ ባለቤት አትሆንም!”

የእስራኤሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንያሚን ኔታንያሁ ትናንት ሰኔ 5 ቀን...

አገር እንዲህ ዓይንህን ለአፈር ይባላል?

በተጀመረው የአለም ዋንጫ ደቡብ አፍሪካ በሜክሲኮ መሸነፏን ተከትሎ አፍሪካ...

አሜሪካ እና ኢራን የመጀመሪያ ደረጃ ስምምነት በ24 ሰዓት ውስጥ እንደሚፈራረሙ ፓኪስታን አስታወቀች

ዩናይትድ ስቴትስ እና ኢራን በሰላም ድርድሩ ማዕቀፎች ላይ መስማማታቸውን...