የመጨረሻዉ ሆስፒታል ስራዉን አቆመ

Date:

በሰሜን ጋዛ የመጨረሻው ሆስፒታል በእስራኤል ትዕዛዝ ስራዉ ለማቆም መገደዱ ተገለፀ።

በሰሜን ጋዛ ግዛት የመጨረሻው የጤና አገልግሎት የሚሰጠው ሆስፒታል የእስራኤል ጦር በአስቸኳይ እንዲለቅ ትዕዛዝ ማስተላለፉን ተከትሎ ከአገልግሎት ውጪ መሆኑን የሆስፒታሉ ዳይሬክተር ተናግረዋል።

ዳይሬክተሩ እንዳሉት ህሙማን ጃባሊያ ከሚገኘው አል-አውዳ ሆስፒታል ወደ ሌላ ስፍራ ተወስደዋል።

እስራኤል እስካሁን በጉዳዩ ላይ የሰጠችዉ ምላሽ ባይኖርም በሆስፒታሉ ያሉ ሰዎች የእስራኤል ጦር ሃይል ሊሰነዝረዉ በሚችለዉ ጥቃት ፈርተዉ መሸሻቸዉን ተናግረዋል።

የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ እርዳታ ኤጀንሲ  እንዳስታወቀው ባለፉት ሁለት ሳምንታት የቀጠለው ግጭት ሆስፒታሉን ጎድቷል፣ ተደራሽነቱን አቋርጧል ብሎም ህሙማን ህክምና እንዳያገኙ አድርጓል።

ከ27 የተባበሩት መንግስታት የፍልስጤም የስደተኞች ኤጀንሲ ጤና ጣቢያ ዘጠኙ በስራ ላይ እንደነበሩ ተመላክቷል።

ኤጀንሲዉ ጋዛን “በምድር ላይ እጅግ የተራበች ቦታ” ሲልም ጠርቷል።

እስራኤል በተያዘዉ የፈረንጆቹ አመት የሁለት ወራት የተኩስ አቁም ስምምነት ካደረገች በኋላ ጥቃቷን በጋዛ አጠናክራ ቀጥላለች።

Nbc_Ethiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አሜሪካ በመካከለኛው ምስራቅ ለሚገኙ ዜጎቿ አስቸኳይ ማስጠንቀቂያ አስተላለፈች

ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ በኢራን ላይ አዳዲስ ወታደራዊ ጥቃቶች ሊሰነዘሩ...

ፍትህ ተሰውቶ የጉልበት ብልጫ የገነነበት ውሳኔ ነው

ለኢትዮጵያ ፕሪሚየር ሊግ ክለቦች የክፍያ ስርዓት መመሪያ (Financial...

“ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ?

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 17ኛ ቀን ውሎ የክልል ተወካዮች ጉባኤ...

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...