የአውሮፓ ሻምፒየንስ ሊግ ፍፃሜ ጨዋታ ዛሬ ምሽት በኢንተር ሚላን እና ፒኤስጂ መካከል ይካሄዳል።
የፍፃሜ ጨዋታው በጀርመን ሙኒክ አሊያንዝ አሬና ስታዲየም ምሽት 4:00 ይጀምራል።
ጨዋታውን ማን ይመራዋል ?
የፍፃሜ ጨዋታውን ሮማኒያዊው ዳኛ እስቴቫን ኮቫችስ በመሀል ዳኝነት እንደሚመሩት ይፋ ሆኗል።
ዋና ዳኛው ከዚህ በፊት ሁለት የፒኤስጂን ጨዋታ ሲመሩ ፒኤስጂ ሁለቱንም ጨዋታዎች ማሸነፍ ችሏል።
በሌላ በኩል ዳኛው በሶስት አጋጣሚዎች የኢንተር ሚላንን ጨዋታ የመሩ ሲሆን ኢንተር ሁለቱን ሲያሸንፍ በአንዱ አቻ ተለያይቷል።
የሁለቱ ክለቦች የእርስበርስ ግንኙነት ?
ኢንተር ሚላን እና ፒኤስጂ ከዚህ በፊት በታሪክ አጋጣሚ በነጥብ ጨዋታ ተገናኝተው አያውቁም።
ጨዋታውን ማን ያሸንፋል ?
@Tikvahethsport @kidusyoftahe
