የረመዳን የበጎ አድራጎት ተግባራት በሌሎች ወራትም መቀጠል ይኖርባቸዋል

Date:

ህዝበ ሙስሊሙ በረመዳን ወቅት ሲያከናውናቸው የቆዩትን የበጎ አድራጎት ተግባራት በሌሎች ወራትም መቀጠል እንዳለበት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ ተናገሩ። 

ሼህ ሀጂ ኢብራሂም ቱፋ 1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን አስመልክቶ ለመገናኛ ብዙሃን መግለጫ ሰጥተዋል።

በመግለጫቸውም፥ ለእምነቱ ተከታዮች እንኳን ለ1 ሺህ 446ኛው ዓመተ ሒጅራ የዒድ አል-ፊጥር በዓል አደረሳችሁ በማለት መልዕክት አስተላልፈዋል።

የረመዳን ወር በአንድነት፣ በፍቅር፣ በአብሮነት፣ በመተጋገዝና በመደጋገፍ ማለፉን ተናግረዋል።

ሕዝበ ሙስሊሙ የዒድ አል-ፊጥር በዓልን ሲያከብር በጾም ወቅት ሲያደርገው እንደነበረው እርስ በርስ በመደጋገፍና ለተቸገሩ ወገኖች በማካፈል ሊሆን እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

ሰላም ለሀገር ሁለንተናዊ ዕድገት ወሳኝ መሆኑን ገልፀው፤ እያንዳንዱ ምዕመን ለዘላቂ ሰላም ግንባታ የበኩሉን መወጣት እንዳለበት ማመልከታቸውን ተዘግቧል ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...

የአህጉሪቱን የርስ በርስ ንግድ ልውውጥ 250 ቢሊዮን ዶላር ለማድረስ ታቀደ

የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና ዋና ፀሐፊ ዋምኬሌ ሜኔ...

በሆርሙዝ ወሽመጥ የሚያልፉ መርከቦች ክፍያ መፈጸም አይጠበቅባቸውም

አሜሪካ እና ኢራን በተስማሙበት የመግባቢያ ሰነድ መሠረት በሆርሙዝ ወሽመጥ...

እስራኤል ጦሯ በደቡብ ሊባኖስ እንደሚቆይ አስታወቀች

የእስራኤል መከላከያ ሚኒስትር እስራኤል ካትዝ እንደተናገሩት፤ በአሜሪካ እና በኢራን...