የሱዳን ጦር በኢትዮጵያ ድንበር አቅራቢያ በብሉ ናይል ግዛት የምትገኘውን የአል ሲልክ አካባቢን ከፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ መቆጣጠሩን ገልጿል።
የሱዳን ጦር አካባቢውን ለመቆጣጠር በተደረገው ውጊያ በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ተዋጊዎችና በአጋሩ የሱዳን ህዝብ የነፃነት እንቅስቃሴ በሰሜን ላይ ከባድ ኪሳራ ደርሷል ብሏል።
የሱዳን ህዝብ የነፃነት እንቅስቃሴ በሰሜን የደቡብ ኮርዶፋንና ብሉ ናይል አካባቢዎች ራስ ገዝ እንዲሆኑ ከ2011 ጀምሮ እየተዋጋ ያለ ነው።
በተያያዘ ዜና የሱዳን ጦር ለሁለት አመት ያህል በፈጥኖ ደራሽ ኃይሉ ስር የነበረችውን ሌላኛዋን የኮርዶፋን ከተማ አል ዳላንጅን የያዘ ሲሆን፣ ውጊያዎች በኮርዶፋን ተባብሰው ቀጥለዋል ተብሏል።
ዘገባው የአናዶሉና ሮይተርስ ነው።
