የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት ከ130 በላይ ለሚሆኑ ሀገራት ለሶማሊላንድ እውቅና እንዲሰጡ ጠየቁ

Date:

የሶማሊላንድ ፕሬዝዳንት አብዲራህማን ሞሀመድ አብዱላሂ ኢሮ ከ130 በላይ ለሚሆኑ ሀገራት ለሶማሊላንድ እውቅና እንዲሰጡ ጥሪ ማቅረባቸውን ገለጹ።

ሶማሊላንድ ነጻነቷን ያወጀችበት 34ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ንግግር ያደረጉት ፕሬዝዳንቱ ጠቅላይ ሚኒስትሮችን ነገሥታትን እና አሚሮችን ጨምሮ ከ130 በላይ ለሚሆኑ ሀገራት ለሶማሊላንድ እውቅና እንዲሰጡ የሚጠይቅ የፕሬዚዳንታዊ ደብዳቤዎችን መላካቸውን ተናግረዋል።

ክብረ በዓል ላይ ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ለሶማሊላንድ የሀገርነት እውቅና እንዲሰጥ በድጋሚ ጠንካራ ጥሪ ማቅረባቸውን ሆርን ዲፕሎማት ዘግቧል።

ፕሬዝዳንት ኢሮ ኢትዮጵያን፣ የተባበሩትአረብኤምሬትስ፣ ዩናይትድ_ኪንግደም፣አሜሪካ፣ጂቡቲ ታይዋን፣ ቱርክ እና ኬንያን ጨምሮ ከሶማሊላንድ ጋር በወዳጅነት ላይ የተመሰረተ ግንኙነት እና ትብብር ላላቸው ሀገሮች ምስጋናቸውን አቅርበዋል።

የሶማሊላንድ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ በሰላም፣ በጋራ መከባበር እና በገንቢ አጋርነት መርሆዎች ላይ የተመሰረተ መሆኑን አረጋግጠው“ በአፍሪካ ቀንድ እና በቀይ ባህር ላይ ብልጽግናን በማጎልበት እና በቀጠናዊ ደህንነት ውስጥ ወሳኝ ሚና ለመጫወት ዝግጁ ነን” ብለዋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...