“የ70 አገራት ዜጎች የህክምና አገልግሎት እያጡ ነው” WHO

Date:

ዓለም አቀፍ ድጋፍ በመቀነሱ ቢያንስ በ70 አገራት የሚኖሩ ዜጎች የህክምና አገልግሎት እያጡ ነው ሲል የዓለም ጤና ድርጅት አስታወቀ፡፡

የድርጅቱ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ቴዎድሮስ አድሀኖም እንዳሉት በድጋፍ መቀዛቀዝ ሳቢያ ታካሚዎች ከኪሳቸው አውጥተው ለመታከም በመገደዳቸው በቂ የህክምና አገልግሎት እያገኙ አይደለም የጤና ተቋማትም ተዘግተዋል ሲሉ አስረድተዋል፡፡

በበርካታ የድጋፍ ሰጪ ተቋማት የሚያገለግሉ የጤና ባለሙያዎችም የስራ ውላቸው ተቋርጦ ቤት ለመቀመጥ ተገደዋል በማለት የችግሩን አሳሳቢነት ገልጸዋል፡፡

የዓለም ጤና ድርጅት ከአጠቃላይ ዓመታዊ በጀቱ የ600 ሚሊዮን ዶላር ጉድለት እንደገጠመው የገለጸ ሲሆን ለቀጣዮቹ ሁለት ዓመታት የሚተገብራቸውን 21 በመቶ ስራዎቹን ለማጠፍ መወሰኑን አስታውቋል ሲል ሮይተርስ ዘግቧል፡፡

የድርጅቱ ዋነኛ የገንዘብ ለጋሽ የነበረችው አሜሪካ በዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ ድጋፏን ለማቋረጥ መወሰኗ ይታወሳል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...

በምክክሩ ሕዝበ ውሳኔ የተጠየቀባቸው ጉዳዮች

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 15ኛ ቀን ውሎ “ስልታዊ” ቡድኖች በተጠናቀሩ...

ንባብ ለሕይወት ባዛር እየተካሄደ ነው !!!

በንባብ ለሕይወት ፕሮጀክትና በኢትዮጵያ ቤተመዛግብትና ቤተመጻሕፍት አገልግሎት አዘጋጅነት የሚካሄደው...

በኢራን የኤነርጂ መሠረተ ልማቶች ላይ ያነጣጠረ አዲስ መጠነ ሰፊ ጥቃት መታቀዱ ተሰማ

የአሜሪካ ጦር በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢራን ላይ አዲስ ጥቃት...