የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በአለም ላይ ያሉ የስደተኞች ቁጥር የሚያሳየዉ “ሁከት የዘመናችን መገበያያ ገንዘብ መሆኑን ነዉ” ብሏል

Date:

የተባበሩት መንግስታት የፀጥታው ምክር ቤት በአለም ላይ እየጨመረ በመጣዉ በስደተኞች ቁጥር በኩል ወቅታዊ መረጃን በዛሬዉ እለት በሰጠበት ወቅት ነዉ ይህንን ያለዉ፡፡

የተባበሩት መንግስታት የስደተኞች ከፍተኛ ኮሚሽነር ፊሊፖ ግራንዲ ለፀጥታው ምክር ቤት ሁኔታዉን ሲገልጹ፤”ሁከት የዘመናችን ዋነኛ መገበያያ ገንዘብ ሆኗል” ሲሉ አስረድተዋል፡፡

ግራንዲ በአለም ዙሪያ በሚሊዮኖች የሚቆጠሩ ሰዎች ተባብሶ በቀጠለው በየሃገሪቱ ባለዉ ግጭቶች ምክንያት ዜጎች ክፉኛ ችግር ዉስጥ ይገኛሉም ብለዋል።

በተለይ ወደ ሰባት ሚሊዮን የሚጠጉ ስደተኞች ከሱዳንና ዩክሬን የተፈናቀሉ መሆናቸዉንም ኮሚሺነሩ ጠቁመዋል፡፡

ኮሚሺነሩ አክለዉም”በአጭርና በረጅም ጊዜ ደህንነታቸው የተጠበቀና አስተማማኝ ዋስትና እስካልተሰጣቸዉ ድርስ ተፈናቃዮችን ወደ ስፍራቸዉ መመለስ አይቻልም” ብለዋል ሲል የዘገበው የአፍሪካ ኒዉስ ።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...