የቲክቶኮ ድምቀት በመድረክ ትያትር መጣ!

Date:



ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው በኢትዮጵያ የድራማ ታሪክ ውስጥ በአዲስ አይነት መንገድ የመጣ ምርጥ ተዋናይ ደራሲና አዘጋጅም ጭምር ነው።

( በአሌክስ ዘመላክ)

ፍላሎት ፣ ትራፊኳና ከአፍ ሰመያመልጥ የተሰኙ ፊልሞች ላይ በመሪ ተዋናይነት ተሳትፏል እንዲሁም አዲስ ድባብ ፤ደባል አማች፤የእቴጌ ማጀት ፤ጎረቤታሞቹ የተሰኙ ተከታታይ የቴሌቪዥን ድራማዎች የተወሰኑት ላይ በፅሁፍ በዝግጅት የተሳተፈ ሲሆን ሁሉም ላይ የትወና አቅሙን አሳይቷል ።


ቴዎድሮስ ከቅርብ ጊዜአት ወዲህ ዘመኑ በፈጠረለት የ ቲክቶክ ፕላትፎርም በመጠቀም እጅግ በተዋበ መንገድ ማህበራዊ፤ ፖለቲካዊና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዩችን በማንሳት በድራማ መልክ በማቅረብ ተወዳጅነትን እያተረፈ ይገኛል።

ባሳለፍነው ሰኞ ሃምሌ 13/2018 ዓም በአለም ሲኒማ የተመረቀው መልቲ ትያትር ላይ ከሌሎች ምርጥ ተዋናዮች ጋር በመሆን ድንቅ ብቃቱን አሳይቷል ።የሰውነቱ ቀጠን ማለት መድረክ ላይ እንዳይታይ አላገደውም ይልቁንም መድረኩ ላይ ገዝፎ ይታያል ።
የኮሜዲ ዘውግ ያለው “መልቲ” ትያትር በመልቲ የትያትር ቡድን ተደርሶ በስንታየሁ ታዬ (ፋቡላ) የተዘጋጀ ነው።


የታሪክ ማጠንጠኛውን በዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ላይ ያደረገው ትያትሩ ከአመታት በፊት በአዲስ አበባ ቴአርትና ባህል አዳራሽ-ማዘጋጃ ቤት ለዕይታ በቅቶ በተመልካቾች ዘንድ ከፍ ያለ አድናቆትና ተወዳጅነትን ማግኘት ችሎም ነበር።

ዘመኑን በሚመጥንና በአዳዲስ ሀሳቦች ዳግም የተዘጋጀው ትያትሩ ምትኩ በቀለ፣ ኤልሻዳይ ከበደ፣ ሱራፌል ብስራት፣ ቴዎድሮስ ሸዋንግዛው፣ አቤል ሰለሞን ፣ እየሩሳሌም ነስሩና ፌቨን ኪዳነ ማሪያም ይተውኑበታል።

መልቲ ዘወትር ሰኞ በ 12:00 ሰዓት በዓለም ሲኒማ ለዕይታ ይበቃል።

ከይትባረክ ገፅ የተወሰደ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ዘመን ባንክ ከ10 ቢሊየን ብር በላይ ያልተጣራ ትርፍ አገኝ

ዘመን ባንክ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከ10.2 ቢሊየን ብር በላይ...

የ8ኛው “ንባብ ለሕይወት!” ዓመታዊ የመጻሕፍት አውደ ርዕይ ጋዜጣዊ መግለጫ

ሐምሌ 20/2018 ዓ.ምበ የኢትዮጵያ ቤተ-መዛግብትና ቤተ-መጻሕፍት አገልግሎት እና ንባብ ለህይወት...

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የ25 ዓመታት ሀገር አቀፍ ማስተር ፕላን ጥናት ይፋ አደረገ

የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት የኃይል አቅርቦት ሥርዓት ወደ ዘመናዊና ዲጂታል...

ኢራን ላይ የተደረገው ጦርነት አሜሪካን እንዳዳከማት ባለስልጣኑ ተናገሩ

የአሜሪካው ኮንግረስ አባል ቶማስ ማሲ፣ የትራምፕ አስተዳደር በኢራን ላይ...