የቻይና ባንክ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ግንባታን በፋይናንስ ለመደገፍ ጠንካራ ፍላጎት እንዳለው ገለጸ

Date:

የኢትዮጵያ አየር መንገድ እና የፋይናንስ ሚኒስቴር ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተ የኢትዮጵያ ልዑክ፤ በአዲሱ ዓለም አቀፍ የአውሮፕላን ማረፊያ ግንባታ የፋይናንስ ድጋፍ ዙሪያ ከቻይና ባንክ ጋር መነጋገሩን የገንዘብ ሚኒስቴር አስታውቋል።

ልዑኩ በውይይቱ ስለ ፕሮጀክቱ ቴክኒካዊ ንድፍ፣ የአፈጻጸም ጊዜ እና አጠቃላይ የፋይናንስ መዋቅር ማብራሪያ መስጠቱ ተጠቁሟል።

“ይህ ፕሮጀክት ኢትዮጵያ በአቪዬሽን ዘርፍ ያላትን መሪነት የሚያጠናክር ከመሆኑም ባለፈ ለንግድ፣ ለቱሪዝም እና ለአጠቃላይ የኢኮኖሚ ዕድገት ቁልፍ ሚና ይጫወታል” ሲል የኢትዮጵያ አየር መንገድ ልዑክ አጽንኦት ሰጥቷል፡፡

የቻይና ባንክ በበኩሉ በፕሮጀክቱ ላይ ያለውን ከፍተኛ ፍላጎት በመግለጽ፤ የፋይናንስ መዋቅሩን ለመረዳት ከፕሮጀክቱ አስተባባሪ የአፍሪካ ልማት ባንክ ጋር ንቁ ግንኙነት መፍጠሩን አረጋግጧል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...