የአለም ባንክ ለኬንያ የቤት ልማት ፕሮጀክት ብድር ሊሰጥ ነው

Date:

የአለም ባንክ ለኬንያ የቤት ግንባታ ፕሮጀክት 1.35 ቢሊየን ዶላር ሊያሰባስብ ሲሆን 375 ሚሊየን ዶላር በብድር መልክ ራሱ ባንኩ ሲሰጣት ከሌሎች አበዳሪዎች 900 ሚሊየን ዶላር ብድር እንድታገኝ ይረዳታል ተብሏል።

በተጨማሪ የነዳጅ ላኪዎች ድርጅት ወይም ኦፔክ ለቤት ግንባታው 75 ሚሊየን ዶላር ይሰጣል ተብሏል።

አለም ባንክ ኬንያ የ2 ሚሊየን ቤቶች እጥረት እንዳለባት አንስቶ ፍላጎቷ በአመት በ250,000 አባወራዎች እየጨመረ እንዳለ ነገር ግን የምታቀርበው ከ50,000 በታች እንደሆነ ገልጿል።

ብድሩ በመጪው ግንቦት ወር እንደሚፀድቅ ሲጠበቅ ዊሊያም ሩቶ በ2027 ሰርተው ለማጠናቀቅ ላቀዷቸው 1 ሚሊየን ቤቶችም ተስፋ የሰጠ ሆኗል።

ዘገባው የኬንያንስ ነው።

@TikvahethMagazine

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...