የአማራ ባንክ  አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ  31.5 ቢሊዮን ብር ደረሰ

Date:

የአማራ ባንክ 2024/25 በጀት አመት ስራ አፈጻጸም ጉባኤ ላይ የባንኩ ወና ስራ አስፈጻሚ ዮሐንስ አያሌው (ዶ/ር) በሪፖርታቸው ይፋ  እንዳደረጉት የባንኩ አጠቃላይ ተቀማጭ ገንዘብ ብር 31.5 ቢሊዮን ማድረስ መቻሉ እና የደንበኞቹን ቁጥር ከ2.4 ሚሊዮን በላይ እንዲሁም የቅርንጫፎቹን ቁጥር 316 ማድረስ ተችሏል፡፡

  ባንኩ በቅርቡ ባስተዋወቀው ለወዳጄ የዲጂታል አነስተኛ ብድር አገልግሎቱ ከ1.6 ቢሊዮን ብር በላይ ከ97 ሺህ በላይ ለሆኑ ደንበኞች ብድር ያቀረበ ሲሆን፤ ከዚህ ውስጥም ሴቶች፣ የአካል ጉዳተኞችና በአነስተኛ ንግድ ሥራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ዋነኞቹ ተጠቃሚ እንደሆኑ  ዋና ሥራ አስፈጻሚው ገልጸዋል፡፡

በበጀት ዓመቱ ባንኩ 70.8 ሚሊዮን የአሜሪካ ዶላር የውጪ ምንዛሬ ማግኘት እንደቻለ ገልጸዋል፡፡ የባንኩ አጠቃላይ ካፒታል 8.6 ቢሊዮን ብር ማድረስ እንደተቻለም አስታውቀዋል፡፡

በብድር አሰባሰብ ረገድ በዓመቱ 10.4 ቢሊዮን ብር መሰብሰብ የተቻለ ሲሆን፣ ይህም ከባለፈው ተመሳሳይ በጀት ዓመት ጋር ሲነፃፀር የ236.3 በመቶ ዕድገት አሳይቷል፡፡

አማራ ባንክ የሰጠው ጠቅላላ የብድር መጠን ከብር 26 ቢሊዮን በላይ ማድረሱንና የተበላሸ የብድር መጠኑ ብሔራዊ ባንክ ካስቀመጠው ከፍተኛ ጣራ በታች መሆኑን የባንኩ ዋና ሥራ አስፈጻሚ ዶ/ር ዮሐንስ ገልጸዋል፡፡

KGEthiopia

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ

የእግዚአብሔር ሕዝብ ጉባኤ፣ የጌታችንና የመድኀኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ አካልና የመንፈስ...

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ ቅርሶች ወደ ኢትዮጵያ ተመልሰዋል

በመቅደላ ጦርነት ጊዜ የተዘረፉ የአጼ ቴዎድሮስ የፀጉር ቁንዳል እና...

ፈረንሳይ የ54 ነጥብ 6 ሚሊዮን ዩሮ ብድር ለመስጠት ተስማምታለች

የፈረንሳዩ ፕሬዚዳንት ኢማኑኤል ማክሮን በኢትዮጵያ ጉብኝታቸው ሀገራቸው ለኢትዮጵያ የኃይል...

ትራምፕ ኢራን ላይ ያላቸው ትዕግሥት እየተሟጠጠ መሆኑን ተናገሩ

የአሜሪካው ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ከቻይናው መሪ ዢ ጂንፒንግ ጋር...