የአሜሪካን ማዕቀብ ፑቲን ማጣጣላቸዉን ተከትሎ የኢኮኖሚ ህመሙ በቅርቡ ይሰማቸዋል ሲሉ ትራምፕ ዛቱ

Date:

የሩሲያ ፕሬዝዳንት ቭላድሚር ፑቲን አሜሪካ በሩሲያ ሁለት ትላልቅ የነዳጅ ኩባንያዎች ላይ ማዕቀብ መጣሏን አጣጠጥለዋል፣ ይህንኑ ተከትሎ የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ እንደተናገሩት የሩሲያው ፕሬዝዳንት በቅርቡ የኢኮኖሚውን ህመም እንደሚሰማቸው ጠቁመዋል።

ትራምፕ በዋይት ሀውስ ለጋዜጠኞች እንደተናገሩት “እንዲህ አይነት ስሜት ስለሚሰማው ደስተኛ ነኝ” ብለዋል። “ይህ ጥሩ ነው ከስድስት ወር በኋላ ስለ ጉዳዩ አሳውቅዎታለሁ፤  ሁሉም ነገር እንዴት እንደሚሄድ እናያለን” ሲሉ ትራምፕ ተደምጠዋል፡፡

ፑቲን በትላንትናዉ እለት በግዙፎቹ የሩሲያ የነዳጅ ኩባንያዎች በሆኑት በሮስኔፍት እና ሉኮይል ላይ የተጣለውን ማዕቀብ “ወዳጅነት የጎደለው ድርጊት” ሲሉ ገልጸው ነገር ግን ድርጊቱ በሩሲያ ኢኮኖሚ ላይ የሚኖረውን ጉዳት አቅልለውታል።”በተፈጥሯቸው ማዕቀቦች ከባድ ናቸው እናም የተወሰነ ውጤት ይኖራቸዋል፤ ነገር ግን በኢኮኖሚያችን ጤና ላይ ምንም አይነት ተጽእኖ አይኖራቸውም” ሲሉ ፑቲን ተደምጠዋል፡፡

ዩናይትድ ስቴትስ ማዕቀቡን ረቡዕ እለት የጣለችው ሞስኮ በዩክሬን ያለውን ጦርነት ለማቆም የሰላም ሂደት ላይ “ከባድ ቁርጠኝነት ስለሌላት ነው” ማለቷ ይታወሳል፡፡

የግምጃ ቤት ዲፓርትመንት በመግለጫው እንዳስታወቀው እርምጃዎቹ የሩስያን የኢነርጂ ዘርፍ “የክሬምሊን ለጦር መሣሪያዎቿ ገቢ የማሳደግ አቅምን ለመጨመር” እና “የተዳከመ ኢኮኖሚዋን ለመደገፍ” ያነጣጠረዉን እንቅስቃሴ ይጎዳል ብሏል።የግምጃ ቤት ፀሐፊ ስኮት ቤሴንት በመግለጫቸው ላይ “ግድያውን ለማስቆም እና የተኩስ ማቆም እንዲደረስ ጊዜው አሁን ነው” ብለዋል።

#ዳጉ_ጆርናል

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

እንግሊዝ ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች ማህበራዊ ሚዲያ እንዳይጠቀሙ አገደች

የእንግሊዝ መንግሥት ዕድሜያቸው ከ16 ዓመት በታች የሆኑ ሕፃናትና ታዳጊዎች...

አሜሪካ 300 ሚሊዮን ዶላር ለኢራን ልትሰጥ ነው መባሉን ትራምፕ አስተባበሉ

አሜሪካ እና ኢራን ከስምምነት ከደረሱ በኋላ አሜሪካ እና አጋሮቿ...

ደህና ሁን! ሰሜ…ስሜ!

“ከልጅነታችን ጀምሮ ጥበብ አገናኝታን ፣ በግሽ አባይ የባህል ቡድን...

✌️ጀግናን ማክበርና መሸለም ጀግንነት ነው

✌️ከዕድሜው የገዘፈው የታሪኩ ጁዋር ጀግናውን ሙሉጌታ ከበደን የመዘከር የጀግንነት...