የአሜሪካ ጦር ኃይሎችን የረዱ አፍጋኒስታናውያን ወደ ሀገራቸው ሊመለሱ ነው

Date:

የትራምፕ አስተዳደር ከአሜሪካ ኃይሎች ጋር አብረው የሠሩ አፍጋኒስታናውያን ወደ አሜሪካ እንዲዛወሩ የረዳውን ቁልፍ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ቢሮ እያፈረሱ ነው ሲል ዘ ዋሽንግተን ፖስት ዘግቧል፡፡

በአሜሪካ የአፍጋኒስታን ቆይታ ወቅት በአስተርጓሚነት፣ ሾፌርነት እና የሲቪል ሠራተኞች ሆነው ያገለገሉትን አብዛኞቹን ጨምሮ ከ250 ሺህ በላይ አፍጋኒስታናውያን በአሁኑ ጊዜ በእንጥልጥል ላይ ይገኛሉ፡፡

በኳታር፣ ፓኪስታን እና በተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች በሚገኙ ካምፖች ውስጥ እንዲቆዩ የተደረጉ አንዳንዶች ደግሞ ታሊባን ወደሚመራት አፍጋኒስታን በግዴታ የመመለስ አደጋ አንዣቦባቸዋል፡፡

የተባበሩት አረብ ኤሚሬቶች፤ አሜሪካ የስደተኞች ማመልከቻ ሂደትን እያዘገየች እና የሎጂስቲክስ ድጋፍ እያቋረጠች መሆኑን ተከትሎ ከአፍጋኒስታን እንዲወጡ የተደረጉ ሰዎችን ወደነበሩበት መመለስ መጀመሯን ለዘ ዋሽንግተን ፖስት የደረሰው መረጃ ያሳያል፡፡

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኢራን ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን በድጋሚ መዝጋቱን የአገሪቱ መገናኛ ብዙኃን ዘገቡ

የኢራን መገናኛ ብዙኃን የአገሪቱ ጦር የሆርሙዝ ወሽመጥን ዳግም መቆጣጠር...

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት ክብረ በዓል

ዋን ፕላኔት ኢንተርናሽናል ስኩል 20ኛ ዓመት የምስረታ በዓሉን አስመልክቶ...

የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ለ20 አትሌቶች  የማስጠንቀቂያ አውጥቷል

በውድድሩ ላይ ያልተገኛችሁ ኢትዮጵያውያን አትሌቶች ይመለከታል የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ዓለምአቀፍ...

የአሜሪካ እና የኢራን ድርድር፤ ለወረራ የታለመ ማደናገሪያ? ሩሲያ ማስጠንቀቂያ ሰጠች!

በአሜሪካ እና በኢራን መካከል የሚደረገው ዲፕሎማሲያዊ ንግግር ውጥረትን ለመቀነስ...