የአርሰናሉ ተጫዋች በሚቀጥለው ሳምንት የኢትዮጵያን ምድር ይረግጣል

Date:

የቀድሞ የአርሰናልና የማን.ሲቲ እንደዚሁም የፈረንሳይ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው ባካሪ ሳኛ በሚቀጥለው ሳምንት ወደ ኢትዮጵያ ሊመጣ ነው።

የቀድሞው የአርሰናል እና የማንችስተር ሲቲ የመስመር ተከላካይ ባካሪ ሳኛ ወደ ኢትዮጵያ በመምጣት ልምዱን እንደሚያካፍል ነው የተነገረው።

ለኢትዮጵያ እግር ኳስ ፌዴሬሽን ከአለም አቀፍ ተቋሞች ጋር ግንኙነት እንዲፈጠር እየሰራ የሚገኘው ዮሀንስ ዘውዱ ወይንም በተለምዶ ጆኒ ቬጋስ አማካኝነት ነው ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ የሚመጣው ተብሏል።

ኢትዮጵያዊው የእግርኳስ ጋዜጠኛ መንሱር አብዱልቀኒ ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ እንደሚመጣም ይፋ አድርጓል።

ተጫዋቹ ወደ ኢትዮጵያ ሲመጣም ከአርሰናል ደጋፊዎች ጋር ይገናኛል የአርሰናል ኦርጅናል ማለያም ያበረክታል ብሏል።

ባካሪ ሳኛ በኢትዮጵያ የሚያደርገው ቆይታ ለምን ያህል ቀን እንደሆነ አልተገለጸም።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

አቶ ዳውድ ኢብሳ ከምርጫው ራሳቸውን አገለሉ

የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) ሊቀመንበር አቶ ዳውድ ኢብሳ በኦሮሚያ...

ኢራን ከአሜሪካ ጋር ‹‹ሁሉን አቀፍ ስምምነት›› እንደምትፈልግ ገለጸች

ኢራን በመካከለኛው ምስራቅ ያለውን ጦርነት ለማቆም ከአሜሪካ ጋር በምታደርገው...

የሪል እስቴት ዘርፍ ዘመናዊ የክፍያ ቴክኖሎጂን ለማስፋፋት አዲስ አጋርነት ፈጠረ

በኢትዮጵያ የሪል እስቴት ዘርፍ ግንባር ቀደም ከሆኑት ድርጅቶች አንዱ...

የአርቲስት ጥላሁን ገሠሠ መታሰቢያ ሐውልት ተመረቀ

ለኢትዮጵያ ዘመናዊ ሙዚቃ ዕድገት ወደር የሌለው አስተዋጽኦ ላበረከተውና የሙዚቃው...