የአርትስ ቴሌቪዥን የስራ ኃላፊዎች ከቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም ሥምምነት ጋር በተያያዘ ማብራሪያ እንዲሰጡ ተጠየቁ

Date:



የአርትስ ቴሌቪዥን የሥራ ኃላፊዎች፣ ከድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) አዲስ አልበም ጋር በተያያዘ ከገቡት ሥምምነት አኳያ ማብራሪያ እንዲሰጡ በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን መጠየቃቸው ተሰምቷል።

ማክሰኞ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ከምሽቱ 12:00 ሰዓት ጀምሮ ሊሰጥ የነበረው የቴዲ አፍሮ አዲስ አልበም “ኢቶሪካ” ጋዜጣዊ መግለጫ በይፋ ታግዷል።

ድምጻዊው ከተለያዩ ጋዜጠኞች ጋር የሚያደርገውን ይህንን መግለጫ በቀጥታ ስርጭት ለማስተላለፍ ከአርትስ ቴሌቪዥን ጋር አስቀድሞ ስምምነት ተፈራርሞ የነበረ ቢሆንም፣ ከመንግስት በቀረበ ጥብቅ እገዳ ምክንያት የቀጥታ ስርጭቱ እንዲቋረጥ ተገዷል።

ማክሰኞ ሚያዝያ 6 ቀን 2018 ዓ.ም ረፋዱ ላይ የቴሌቪዥን ጣቢያው ስራ አስፈፃሚን ጨምሮ የጣቢያው ስራ ኃላፊዎች በኢትዮጵያ መገናኛ ብዙሃን ባለስልጣን ዋና መስሪያ ቤት በመገኘት ስለ ሥምምነቱ ማብራሪያ ሰጥተዋል።

ድምጻዊ ቴዎድሮስ ካሳሁን ከስምንት ዓመታት ቆይታ በኋላ ‘ኢቶሪካ’ የተሰኘውን አዲስ አልበሙን የፊታችን ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2018 ዓ.ም ከቀኑ 8፡00 ሰዓት ጀምሮ በተለያዩ ዓለም አቀፍ የሙዚቃ ማሰራጫ መተግበሪያዎች እና በዩቲዩብ ገጹ በኩል ለአድማጮች እንደሚያቀርብ ማስታወቁ ይታወሳል።

የመግለጫው መታገድ እና የቴሌቪዥን ጣቢያው ኃላፊዎች መጠራት በአልበሙ ይፋ መሆን ላይ ስለሚኖረው ተጽዕኖ እስካሁን በይፋ የተባለ ነገር የለም።

ዋዜማ

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የአዳዲስ እና የሁለተኛ ዙር መራጮች አቅምና ሚና

ግዮን መጽሔት :- በ7ኛው አገራዊ ምርጫ ላይ የአዳዲስ (ለመጀመሪያ...

በ’ፊንቴክ’ የማጭበርበር ወንጀል በተጠረጠሩት ላይ ተጨማሪ ቀጠሮ ተሰጠ

በ"ፊንቴክ" ኢንቨስትመንት ስም በተፈጸመ  የማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው በቁጥጥር ስር...

የጣሊያን ኩባንያዎች በኢትዮጵያ ያደረጉት የኢንቨስመንት መጠን 723 ሚሊዮን ዩሮ መድረሱ ተሰማ

ከ20 በላይ የጣሊያን ኩባንያዎች  በአዲስ አበባ ዓለም አቀፍ ኮንቬንሽን...

የቴሌግራም ማስጠንቀቂያ

ቴሌግራም (Telegram) ኦፊሴላዊ ያልሆኑ የቴሌግራም መተግበሪያዎችን (Unofficial Apps) በሚጠቀሙ...