የተፈናቃዮች ቁጥር ከዘጠኝ ሺህ በላይ መሆኑን የደቡብ ምዕራብ ሸዋ ዞን ኮምንኬሽን ጽህፈት ቤት አስታውቋል።
የጽ/ቤቱ ኃላፊ ወይዘሮ ኤቢሴ ተርፋ ዛሬ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ እንደገለፁት የዛሬን ማለትም የነሀሴ 1 ቀን 2017 ዓ .ም መረጃን ሳይጨምር ከወንዙ መሙላት ጋር በተያያዘ ከዘጠኝ ሽህ በላይ ሰዎች ተፈናቅለዋል።
የተፈናቀሉት ዜጎችም በሁለት ወረዳዎች በትምህርት ቤቶች ውስጥ ተጠልለው የምግብ እና የመኝታ እርዳታ እየተደረገላቸው ይገኛል ብለዋል።
” አሁንም የውሃው መጠን እየጨመረ ነው ” ያሉት ኃላፊዋ ከፍተኛ ትኩረት ይሻል ሲሉም አክለዋል።
