የአዲስ አበባ መታወቂያ የአገልግሎት ዘመን እና ሌሎች ማሻሻያዎች ሊደረጉለት  ነው

Date:

የከተማዋ የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ እንዳስታወቀው በቀጣይ ወራት በስራ ላይ ያለውን  የነዋሪነት መታወቂያ ይዘት፣ የአገልግሎት ዘመን እና የገፅ ዲዛይን ከተማዋ ያለችበትን ደረጃ በሚመጥን እና ፋይዳን መሰረት ባደረገ እንዲሁም ሁሉን አቀፍ አገልግሎት የሚሰጥ /  Smart  Card/  አድርጎ ለማሻሻል ዝግጅት እያደረገ እንደሚገኝም አስታውቋል።

በተጨማሪም  ተቋሙ ለ 2 ሚሊዮን ነዋሪዎች የዲጂታል ካርድ መታወቂያን  መሰጠቱን ገልፆል።

ይህ የመታወቂያ የዲጂታል ምዝገባ የነዋሪን የባዮሜትሪክ መረጃን ያካተተ  እና ከ35 በላይ  ለማስረጃነት ጥቅም ላይ የሚውሉ የግለሰብ መረጃዎች  የሚመዘገቡበት ስርዓት መሆኑን ኢትዮ ኤፍኤም ከተቋሙ ያገኘው መረጃ  ይጠቁማል።

የሲቪል ምዝገባ እና የነዋሪነት አገልግሎት ኤጀንሲ የወረቀት መታወቂያ መስጠትን ለመጨረሻ ግዜ ማብቃቱን እና  ሙሉ ለሙሉ ወደ ዲጂታል ሽግግር መደረጉን  ባለፈው ሰኔ 25/2016ዓ.ም ይፋ ማድረጉን በመረጃው  አስታውሷል።

በተቋሙ የወሳኝ ኩነት ምዘገባን ጨምሮ በጠቅላላው ወደ 3 ሚልዮን የሚጠጉ ነዋሪዎች መረጃ በዲጂታል ምዘገባ የመረጃ ቋት ውስጥ እንዳለም አመላክቷል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

“ተፅዕኖ ፈጣሪዎች” የተባሉ ግለሰቦች በምክክሩ እንዲሳተፉ በምን መስፈረት ተመረጡ?

በሀገራዊ የምክክር ጉባኤ 17ኛ ቀን ውሎ የክልል ተወካዮች ጉባኤ...

የአሜሪካ ጦር እስራኤልን ከኢራን መከላከሌን ላቆም እችላለሁ አለ

በመካከለኛው ምስራቅ ያለው ውጥረት በከፍተኛ ሁኔታ በናረበት በዚህ...

በፌደራሉ ሠራዊት እና በትግራይ ኃይሎች መካከል ግጭት መቀስቀሱ ተገለጸ

ከሱዳን ጋር በሚዋሰነው የሰሜናዊ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክፍል ውስጥ በሚገኝ...

ሳፋሪኮም በኢትዮጵያ ለሚገኘው ቅርንጫፉ ተጨማሪ 1.4 ቢሊዮን ሺሊንግ ኢንቨስት አደረገ

የኬንያው የቴሌኮም ግዙፍ ኩባንያ ሳፋሪኮም እስከ ሰኔ 2018 ዓ.ም...