በመርሐ ግብሩ ላይ የተገኙት ፕሬዚዳንት ታዬ አጽቀስላሴ የቀይ መስቀል ማህበር የፎቶ ግራፍ አውደ ርዕዩን ከፍተዋል።
ዕለቱ “ለዘጠና ዓመታት የተሻገር የሰብዓዊ አገልግሎት አሻራ” በሚል መሪ ሀሳብ ነው እየተከበረ የሚገኘው።
ማህበሩ ዘጠና ዓመቱን ሲያከብር የተጓዘበትን የሰብዓዊ ድጋፍ አገልግሎት በፎቶና በምስል ለዕይታ ቀርቧል።
በበጎ ፍቃድ አገልግሎት ለተሳተፉ ተቋማትና በጎ ፍቃደኞች እውቅና እንደሚሰጥ የተቋሙ የስራ ሃላፊ ተናግረዋል።
