የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 27ኛውን ዙር የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ሊያካሂድ ነው

Date:

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ 125 ሚሊዮን ዶላር መደበኛ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ ረቡዕ ነሐሴ 20 ቀን 2018 ዓ.ም. እንደሚካሄድ አስታውቋል።

ባንኩ ይህንን የውጭ ምንዛሬ ጨረታ የሚያካሄደው  ቀናት በፊት ነሐሴ 14 ቀን 2018 ዓ.ም. ካካሄደው 500 ሚሊዮን ዶላር ልዩ የውጭ ምንዛሬ ጨረታ በኋላ ነው።

ማዕከላዊ ባንኩ በወቅቱ ባካሄደው የገንዘብ ፖሊሲ ትግበራ ልዩ ጨረታ ከንግድ ባንኮች የ710 ሚሊዮን ዶላር ከፍተኛ ፍላጎት የቀረበ ሲሆን፤ ከተሳተፉት 22 ንግድ ባንኮች ውስጥ 21ዱ የዶላር ድልድል ማግኘት ችለዋል።

በዕለቱም ባንኩ ባከናወነው በዚህ ጨረታው የአንድ ዶላር አማካኝ ዋጋ 160.21 ብር ሆኖ መመዝገቡ ይታወሳል። ይህም ከቀድሞው መደበኛ ጨረታ ጋር ሲነጻጸር የብር የመግዛት አቅም በአንድ በመቶ ገደማ ከዶላር አንፃር እንዲጠናከር አስችሏል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

ካናዳ ምዝገባም ሆነ ስምሪት አልተጀመረም

የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር መቀመጫውን ካናዳ ካደረገው "ፊውቸር ፊት ኢንተርናሽናል"...

የክቡር ዶክተር ጋሽ መሐሙድ አዲስ አልበም ለአድማጮች ሊደርስ ነዉ

ታዋቂው ድምፃዊ ክቡር ዶክተር አርቲስት መሐሙድ አሕመድ «ለታሪክ» የተሰኘውንና...

ሜታ ‘ፌስቡክ እና ኢንስታግራም በቀረበባቸው ክስ 18 ቢሊዮን ዶላር ለመክፈል ተስማማ

ግዙፉ የማኅበራዊ ሚዲያ ኩባንያ ሜታ በፌስቡክ እና በኢንስታግራም ምክንያት...