የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለሀገር ውስጥ በረራ አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኘው በኪሳራ እንደሆነ እና ማትረፍ አለመጀመሩን አስታውቋል።
የአየር መንገዱ ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ መስፍን ጣሰው: ተቋሙ ባለፈው ዓመት በሀገር ውስጥ በረራ ምክንያት 28 ሚሊየን ዶላር ኪሳራ ማስተናገዱን ተናግረዋል።
ኪሳራው ያጋጠመው በቅርቡ በተደረገው የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ምክንያት በውጭ ምንዛሬ ገበያ ላይ ለታየው ለውጥ ተመጣጣኝ የሆነ የዋጋ ጭማሪ በሀገር ውስጥ በረራዎች ላይ ባለመደረጉ ነው ተብሏል።
ዋና ሥራ አስፈጻሚው የ2018 ዓ.ም. የግማሽ ዓመት የሥራ አፈጻጸምን አስመልክቶ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ አየር መንገዱ አሁንም ትርፍ ማግኘት ባይቻልም በበጀት ዓመቱ የመጀመሪያ 6 ወራት የኪሳራው መጠን በከፍተኛ ሁኔታ መቀነሱን አብራርተዋል።
ተቋሙ በሀገር ውስጥ በረራዎች እያጋጠመው የሚገኘውን ኪሳራ ቀስ በቀስ ለማስወገድ በበረራ ትኬቶች ላይ ደረጃ በደረጃ የዋጋ ማስተካከያዎች እያደረገ እንደሆነ ተጠቁሟል።
