የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ በግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ ላይ መሳተፍ ጀመረ

Date:

ብሄራዊ ባንክ እያደረገ ካለው ለውጥ መካከል የግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታን ማዘመን እና ከፋይናንስ ኩባንያዎች ባሻገር ተጨማሪ ተጫራቾች እንዲሳተፉ መሳብ ይገኝበታል፡፡

በዚህም መሰረት ግዙፍ የመንግስት ቢዝነስ ተቋማተትን የያዘው የኢትዮጵያ ኢንቨስትመንት ሆልዲን በየ15 ቀኑ በሚደረገው የግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታ (የመጀመሪያ ደረጃ የገንዘብ ገበያ) ተሳታፊ መሆን መጀመሩን አስታውቋል፡፡

በዚህም በመጀመሪያው የጨረታ ተሳትፎ 7 ቢሊየን ብር የሚያወጣ ቦንድ መግዛቱን ነው የኢንቨስትመንት ሆልዲንግ ያስታወቀው፡፡

የግምጃ ቤት ሰነድ ጨረታን ለገንዘብ ሚኒስቴር በውክልና የሚያካሂደው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ባንክ መሆኑ ይታወሳል፡፡

ሰነድ ተሸጦ የሚገኘው ገንዘብ ለበጀት ጉድለት ማሟያ የሚያገለግል ሲሆን በተለይ መንግስት ከብሄራዊ ባንክ የሚወስደውን የቀጥታ ብድር እንዲቀንስ ወይም እንዲያቆም የሚያግዝ በመሆኑ የዋጋ ንረትን ለመከላከል አይነተኛ መሳሪያ መሆኑ ይነገርለታል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የተፈናቀሉ ዜጎች በተጠለሉበት አካባቢ በቋሚነት መኖር የሚያስችላቸው 

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ደቡብ ኦሞ ዞን የዳሰነች ወረዳ ከበኦሞ...

ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ 11ኛውን የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርት በደብረ ብርሃን ከተማ አስመረቀ

ታዋቂው አትሌትና ባለሀብት ሻለቃ ኃይሌ ገብረሥላሴ፣ በደብረ ብርሃን ከተማ...

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር የተዘጋጀው የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል ስቴት ኤግዘቢሽን ተከፈተ

በኢትዮጵያ ሪል ስቴት አልሚዎች ማህበር አዘጋጅነት የመጀመሪያው አህጉራዊ የሪል...

በሊባኖስ እና በእሰራኤል የተደረሰው የተኩስ አቁም ስምምነት ተራዘመ

ትራምፕ በሊባኖስ እና በእሰራኤል መካከል የተደረሰው የተኩስ አቁም በሦስት...