የጋዛው ጦርነት ፍጹም ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ነው

Date:

የሮማ ካቶሊክ ርዕሰ ሊቀ ጳጳስ ፖፕ ሊዮ 14ተኛ በጋዛ ምግብ እና እርዳታ እየጠበቁ ያሉ ዜጎች ላይ እስራኤል ጥቃት አድርሳለች፤ በርካታ ፍልስጤማውያንም ሕይወታቸው አልፏል ብለዋል።

ፖፕ ሊዮ አክለውም የዓለም ዓቀፉ ማሕበረሰብ በጋዛ እየደረሰ ያለውን ጭካኔያዊ ድርጊት እንዲቆም እጠይቃለሁ፣ ሰላም ሊሰፍን ይገባል ሲሉም አስምረውበታል።

እስራኤል በበኩሏ አሁንም በመሐል ጋዛ ያሉ ዜጎች በአስቸኳይ ስፍራውን ለቀው እንዲወጡ ትእዛዝ ሰጥታለች።

በተያያዘም ከራፋህ እና ከዴይር አል ባላህ ዜጎች እንዲወጡ እየተገደዱም ሲሆን፣ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በበኩሉ ይህ ትእዛዝ 85 ሺህ ሕዝቦችን የሚጎዳ ነው ብሏል።

ድርጅቱ ለአዲስ ተፈናቃዮች ሰብአዊ እርዳታን በማድረስ ዙርያም ከእስራኤል ባለሥልጣናት ጋር እየመከረበት እንደሆነ አስታውቋል።

ያጋሩ!

መጽሔቶች

በብዛት የተነበቡ

ተጨማሪ ጽሑፎች
ተመሳሳይ

የኮሪያ ዘማቾች ያስመዘገቡት አኩሪ ታሪክ በዓለም ሲታወስ ይኖራል

75ኛ ዓመት የኮሪያ ዘማቾች መታሰቢያ በዓል አዲስ አበባ በሚገኘው...

አሜሪካ በጣለችው የባህር ላይ እገዳ ሳቢያ ኢራን 4.8 ቢሊዮን ዶላር አጣች

በአሜሪካው ፕሬዝዳንት ዶናልድ ትራምፕ ትዕዛዝ በኦማን ባህረ ሰላጤ ላይ...

ኢሕአፓ ሊያካሂድ የነበረውን ሰላማዊ ሰልፍ ማራዘሙን አስታወቀ

የኢትዮጵያ ህዝቦች አብዮታዊ ፓርቲ (ኢሕአፓ) ሚያዚያ 30 ቀን 2018...

እሁድ መንገዶች ለተሽከርካሪዎች ዝግ ይደረጋሉ

መነሻውንና መድረሻውን መስቀል አደባባይ የሚያደረገው ዓለም አቀፉ የዛይድ የበጎ...